ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 5 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ስለ ወይን ቦታ የተነገረ ቅኔ

1. ስለ ወዳጄ፣ደግሞም ስለ ወይን ቦታው ልዘምር፤ወዳጄ በለምለም ኰረብታ ላይየወይን ቦታ ነበረው።

2. መሬቱን ቈፈረ፤ ድንጋይንም ለቅሞ አወጣ፤ምርጥ የሆነውንም ወይን ተከለበት።በመካከሉ መጠበቂያ ማማ ሠራ፤የወይን መጭመቂያ ጒድጓድም አበጀ፤ከዚያ መልካም ፍሬ ያፈራል ብሎ አሰበ፤ነገር ግን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ።

3. “እናንት በኢየሩሳሌም የምትኖሩና የይሁዳ ሰዎች ሆይ፤በእኔና በወይኔ ቦታ መካከል እስቲ ፍረዱ።

4. ከዚህ ካደረግሁለት በላይ ለወይኔ ቦታ ምንሊደረግለት ይገባ ነበር?መልካም የወይን ፍሬ ያፈራል ብዬስጠብቅ ለምን ኮምጣጣ ፍሬ አፈራ?

5. እንግዲህ በወይኔ ቦታምን እንደማደርግ ልንገራችሁ፤ዐጥሩን እነቅላለሁ፤ለጥፋት ይጋለጣል፤ግንቡንም አፈርሳለሁ፣መረጋገጫም ይሆናል።

6. የማይኰተኰትና የማይታረምጠፍ መሬት አደርገዋለሁ፤ኵርንችትና እሾኽም ይበቅልበታል፤ዝናብም እንዳይዘንብበትደመናዎችን አዝዛለሁ።”

7. የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርየወይን ቦታው የእስራኤል ቤት ነው፤የይሁዳ ሰዎችምየደስታው አትክልት ናቸው።ፍትሕን ፈለገ፤ ነገር ግን ደም ማፍሰስን አየ፤ጽድቅን ፈለገ፤ ነገር ግን የጭንቅን ጩኸት ሰማ።

ወዮታና ፍርድ

8. ስፍራ ለሌሎች እስከማይተርፍ፣ቤትን በቤት ላይ በመጨመር፣መሬትን ከመሬት ጋር በማያያዝ፣ለብቻችሁ በምድር ተስፋፍታችሁ ለምትኖሩ ወዮላችሁ

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ጆሮዬ እየሰማ እንዲህ ሲል ተናገረ፤“ታላላቅ ቤቶች ወና ይቀራሉ፣የሚያማምሩም ቤቶች ኗሪ ያጣሉ።

10. ከሩብ ጋሻ የወይን ቦታ አንድ የባዶስ መስፈሪያ ያህል የወይን ጭማቂ ብቻ ይገኛል፤ አንድ የቆሮስ መስፈሪያ ዘር ተዘርቶ አንድ የኢፍ መስፈሪያ እህል ብቻ ይሰጣል።

11. የሚያሰክር መጠጥ ፍለጋማልደው ለሚነሡ፣እስኪያነዳቸውም ወይን በመጠጣትሌሊቱን ለሚያነጉ ወዮላቸ

12. በግብዣቸው ላይ በገናና መሰንቆ፣ከበሮና ዋሽንት እንዲሁም የወይን ጠጅ አለ፤ነገር ግን ለእግዚአብሔር ሥራ ቦታ አልሰጡም፤ለእጆቹም ሥራ ክብር አላሳዩም።

13. ስለዚህ ሕዝቤዕውቀት በማጣቱ ይማረካል፤መኳንንቱም በራብ ይሞታሉ፤ሕዝቡም በውሃ ጥም ይቃጠላል።

14. ስለዚህ ሲኦል ሆዷን አሰፋች፣አፏንም ያለ ልክ ከፈተች፤መኳንንቱና ሕዝቡ ከረብሸኞቻቸውና ከጨፋሪዎቻቸው ጋርወደዚያ ይወርዳሉ።

15. ሰው ይዋረዳል፤የሰው ልጅም ዝቅ ዝቅ ይላል፤የእብሪተኛውም ዐይን ይሰበራል።

16. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ግን በፍትሕ ከፍ ከፍ ይላል፤ቅዱሱም አምላክ ቅድስናውን በጽድቅ ይገልጻል።

17. በጎችም በገዛ መሰማሪያቸው እንደሚሰማሩ ሆነው ይግጣሉ፤የበግ ጠቦቶችም በባለጠጎች ፍርስራሽ ላይ ሣር ይበላሉ።

18. ኀጢአትን በማታለል ገመድ ለሚስቡ፣በደልንም በሠረገላ ማሰሪያ ለሚጐትቱ ወዮላቸው!

19. በዐይናችን እንድናይ እግዚአብሔር ይቸኵል፤ሥራውንም ያፋጥን፤የእስራኤልን ቅዱስ፣ የእርሱን ዕቅድእንድናውቃት ትቅረብ፤ትምጣም ለሚሉ ወዮላቸው!”

20. ክፉውን መልካም፣መልካሙን ክፉ ለሚሉብርሃኑን ጨለማ፣ጨለማውን ብርሃን ለሚያደርጉ፣ጣፋጩን መራራ፣መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው!

21. ራሳቸውን እንደ ብልኅ ለሚቈጥሩ፣በራሳቸውም አመለካከት ጥበበኛ ለሆኑ ወዮላቸው!

22. የወይን ጠጅ ለመጠጣት ጀግኖች፣የሚያሰክር መጠጥ ለመደባለቅ ብርቱ ለሆኑ ወዮላቸው!

23. ጒቦን በመቀበል በደለኛን ንጹሕ ለሚያደርጉ፣ለበደል አልባ ሰው ፍትሕን ለሚነፍጉ ወዮላቸው!

24. ስለዚህ የእሳት ነበልባል ገለባን እንደሚበላ፣ድርቆሽም በእሳት ጋይቶ እንደሚጠፋ፣የእነርሱም ሥር እንዲሁ ይበሰብሳል፤አበባቸውም እንደ ትቢያ ይበናል፤የሰራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ሕግ ንቀዋልና፤የእስራኤል ቅዱስ የተናገረውንም ቃል አቃለዋል።

25. የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነዶአል፤እጁን አንሥቶ መቶአቸዋል፤ተራሮች ራዱ፤ሬሳዎችም በመንገድ ላይ እንደተጣለ ጥራጊ ሆኑ፤ይህ ሁሉ ሆኖ ግን ቍጣው ገና አልተመለሰም፤እጁም እንደ ተነሣ ነው።

26. ከሩቅ ያሉትን ሕዝቦች የሚጠራበትንምልክት ያቆማል፤ከምድር ዳርቻም በፉጨት ይጠራቸዋል፤እነርሱም እየተጣደፉ በፍጥነት ይመጣሉ።

27. በመካከላቸው ደካማና ስንኩል አይገኝም፤የሚያንቀላፋና የሚተኛ አይኖርም፤የወገባቸው መቀነት አይላላም፤የጫማቸውም ማሰሪያ አይበጠስም።

28. ፍላጻቸው የተሳለ፣ቀስታቸውም የተደገነ ነው፤የሠረገሎቻቸውም መንኰራኵሮች እንደዐውሎ ነፋስ ናቸው።

29. ጩኸታቸው እንደ አንበሳ ነው፤እንደ አንበሳ ደቦል ያገሣሉ፤ያደኑትንም ይዘው ይጮኻሉ፤ተሸክመውት ይሄዳሉ፤ የሚያስጥልም የለም።

30. በዚያን ቀንእንደ ባሕር ሞገድ ይጮኹበታል፤ማንም ወደ ምድር ቢመለከት፣ጨለማንና መከራን ያያል፤ብርሃን እንኳ በደመናዎች ይጋረዳል።