ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ለያዕቆብ ይራራለታል፤እስራኤልን እንደ ገና ይመርጠዋል፤በራሳቸውም አገር ያኖራቸዋል።መጻተኞች አብረዋቸው ይኖራሉ፤ከያዕቆብም ቤት ጋር ይተባበራሉ።

2. አሕዛብም ይወስዷቸዋል፤ወደ ገዛ ስፍራቸውም ይመልሷቸዋል።የእስራኤል ቤት አሕዛብን ርስት ያደርጓቸዋል፤ በእግዚአብሔርም ምድር ወንዶችና ሴቶች ባሪያዎች አድርገው ይገዟቸዋል፤የማረኳቸውን ይማርኳቸዋል፤የጨቈኗቸውንም ይገዟቸዋል።

3. እግዚአብሔር ከሥቃይህ፣ ከመከራህና ከጽኑ ባርነትህ ባሳረፈህ ቀን፣

4. በባቢሎን ንጉሥ ላይ ትሣለቃለህ፤ እንዲህም ትላለህ፤ጨቋኙ እንዴት አበቃለት!አስገባሪነቱስ እንዴት አከተመ!

5. እግዚአብሔር የክፉዎችን ዘንግ፣የገዦችንም በትረ መንግሥት ሰብሮአል፤

6. ሕዝቦችን በማያቋርጥ ቍጣ የመታውን፣ያለ ርኅራኄ እያሳደደየቀጠቀጠውን ሰብሮአል።

7. ምድር ሁሉ ሰላምና ዕረፍት አግኝታለች፤የደስታም ዝማሬ ታስተጋባለች።

8. ጥድና የሊባኖስ ዝግባ እንኳ ደስ ብሎአቸው፣“አንተም ወደቅህ፤ዕንጨት ቈራጭምመጥረቢያ አላነሣብንምቃ አሉ።

9. በመጣህ ጊዜሲኦል ልትቀበልህ ተነሣሥታለች፤ይቀበሉህም ዘንድ የሙታንን መናፍስት፣በዓለም ገዥ የነበሩትን ሁሉ ቀስቅሳለች፤በአሕዛብ ላይ የነገሡትን ነገሥታትከዙፋናቸው አውርዳለች።

10. እነርሱ ሁሉ ይመልሱልሃል፤እንዲህም ይሉሃል፤“አንተም እንደ እኛ ደከምህ፤እንደ እኛም ሆንህ።”

11. ክብርህ፣ ከነበገና ድምፁወደ ሲኦል ወረደ፤ብሎች ከበታችህ ተነጥፈዋል፤ትሎችም መደረቢያህ ይሆናሉ።

12. አንተ የንጋት ልጅ፣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፤እንዴት ከሰማይ ወደቅአንተ ቀድሞ መንግሥታትን ያዋረድህ፤እንዴት ወደ ምድር ተጣልህ!

13. በልብህም እንዲህ አልህ፤“ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፤ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ አደርጋለሁ፤በተራራው መሰብሰቢያ፣በተቀደሰውም ተራራ ከፍታ ላይ በዙፋኔእቀመጣለሁ፤

14. ከደመናዎችም ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፤ራሴንም እንደ ልዑል አደርጋለሁ።”

15. ነገር ግን ወደ ሲኦል፣ወደ ጥልቁም ጒድጓድ ወርደሃል።

16. የሚያዩህም አትኵረው እየተመለክቱህ፣በመገረም ስለ አንተ እንዲህ ይላሉ፤“ያ ምድርን ያናወጠ፣መንግሥታትን ያንቀጠቀጠ፣ ይህ ሰው ነውን?

17. ዓለምን ምድረ በዳ ያደረገ፤ከተሞችን ያፈራረሰ፣ምርኮኞቹንም ወደ አገራቸው እንዳይሄዱ የከለከለ ይህ ነውን?”

18. የአሕዛብ ነገሥታት ሁሉ በክብር አንቀላፍተዋል፤በየመቃብራቸው ዐርፈዋል።

19. አንተ ግን እንደማይፈለግ ቅርንጫፍ፣ከመቃብር ወጥተህ ተጥለሃል፤በሰይፍ በተወጉት፣ወደ ጥልቁ ድንጋዮች በወረዱት፣በተገደሉትም ተሸፍነሃል።እንደ ተረገጠም ሬሳ ሆነሃል።

20. ከእነርሱ ጋር በመቃብር አትሆንም፤ምድርህን አጥፍተሃልና፤ሕዝብህንም ፈጅተሃልና።የክፉ አድራጊዎች ዘርፈጽሞ አይታወስም።

21. ተነሥተው ምድርን እንዳይወርሱ፣ዓለምንም በከተሞቻቸው እንዳይሞሉ፣ስለ አባቶቻቸው ኀጢአት፣ወንድ ልጆቹ የሚታረዱበትን ስፍራ አዘጋጁ።

22. “በእነርሱ ላይ እነሣለሁ”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።“ስሟንና ትሩፋኖቿን፣ዘሯንና ትውልዷን ከባቢሎን እቈርጣለሁ”ይላል እግዚአብሔር።

23. “የጃርት መኖሪያ፣ረግረጋማ ቦታ አደርጋታለሁ፤በጥፋትም መጥረጊያ እጠርጋታለሁ”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

በአሦር ላይ የተነገረ ትንቢት

24. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ምሎአል፤“እንደ ዐቀድሁት በርግጥ ይከናወናል፤እንደ አሰብሁትም ይሆናል።

25. አሦርን በምድሬ ላይ አደቃለሁ፤በተራራዬም ላይ እረግጠዋለሁ፤ቀንበሩ ከሕዝቤ ላይ ይነሣል፤ሸክሙም ከትከሻቸው ላይ ይወርዳል።”

26. ለምድር ሁሉ የታሰበው ዕቅድ ይህ ነው፤በአሕዛብም ሁሉ ላይ የተዘረጋው እጅ ይኸው ነው።

27. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ አስቦአል፤ማንስ ያግደዋል?እጁም ተዘርግቶአል?ማንስ ይመልሰዋል?

በፍልስጥኤማውያን ላይ የተነገረ ትንቢት

28. ንጉሡ አካዝ በሞተበት ዓመት እንዲህ የሚል ንግር መጣ፤

29. “እናንት ፍልስጥኤማውያን ሆይ፤የመታችሁ በትር ስለ ተሰበረ ሁላችሁ ደስ አይበላችሁ፤ከእባቡ ሥር እፉኝት ይወጣልና፤ፍሬውም ተወርዋሪ መርዘኛ እባብ ይሆናል።

30. ከድኻም ድኻ የሆኑት መሰማሪያ ያገኛሉ፤ችግረኞችም ተዝናንተው ይተኛሉ፤ሥርህን ግን በራብ እገድላለሁ፤ትሩፋንህንም እፈጃለሁ።

31. በር ሆይ፣ ዋይ በል፤ ከተማ ሆይ ጩኽ፣ፍልስጥኤማውያን ሆይ፤ ሁላችሁም በፍርሀት ቅለጡጢስ ከሰሜን መጥቶብሃል፤ከሰልፉ ተነጥሎ የሚቀር የለምና።

32. ከዚያ ሕዝብ ለሚመጡ መልእክተኞች ምን መልስ ይሰጣል?መልሱ፣ “እግዚአብሔር ጽዮንን መሥርቶአል፤መከራን የተቀበለው ሕዝብም፣በእርሷ ውስጥ መጠጊያን አግኝቶአል” የሚል ነው።