ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ወዮ ለእምቢተኛ ሕዝብ

1. “ለዐመፀኞች ልጆች ወዮላቸው”ይላል እግዚአብሔር፤“የእኔ ያልሆነውን ሐሳብ ይከተላሉ፤ከመንፈሴ ያልሆነውን ቃል ኪዳን ያደርጋሉ፤በኀጢአት ላይ ኀጢአት ይጨምራሉ።

2. እኔን ሳይጠይቁ፣ወደ ግብፅ ይወርዳሉ፤የፈርዖንን ከለላ፣የግብፅንም ጥላ ለመጠጊያነት ይፈልጋሉ።

3. ነገር ግን የፈርዖን ከለላ ውርደት ይሆንባችኋል፤የግብፅም ጥላ ኀፍረት ያመጣባችኋል።

4. ምንም እንኳ ሹሞች በጣኔዎስ ቢኖሯቸውም፣መልእክተኞቻቸው ሓኔስ ቢደርሱም፣

5. ውርደትና ኀፍረት ብቻ እንጂርዳታም ሆነ ረብ በማያስገኙላቸውምንም ጥቅም በማይሰጧቸው ሰዎች ምክንያትሁሉም ለኀፍረት ይዳረጋሉ።”

6. በኔጌቭ ስላሉት እንስሳት የተነገረ ንግር፤መልእክተኞች ሀብታቸውን በአህያ፣ውድ ዕቃዎቻቸውን በግመል ጭነው፣ተባዕትና እንስት አንበሶች፣መርዘኛና ተወርዋሪ እባቦች በሚኖሩበት፣መከራና ጭንቅ ባለበት ምድር ዐልፈው፣ወደማይጠቅማቸው ወደዚያ ሕዝብ፣

7. ርዳታዋም ፈጽሞ ዋጋ ቢስ ወደ ሆነው ወደ ግብፅ ይሄዳሉ።ስለዚህ ስሟን፣ረዓብ፣ ምንም የማትጠቅም ብዬ እጠራታለሁ።

8. አሁንም ሂድ፤ በሰሌዳ ላይ ጻፍላቸው፤በጥቅልል መጽሐፍ ላይ ክተብላቸው፤ለሚመጡትም ዘመናት፣ለዘላለም ምስክር ይሆናል፤

9. እነዚህም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለመስማት የማይፈልጉ፣ዐመፀኛ ሕዝቦችና አታላይ ልጆች ናቸው።

10. ባለ ራእዮችን፣“ከእንግዲህ ራእይን አትዩ” ይላሉ፤ነቢያትንም እንዲህ ይላሉ፤“እውነተኛውን ትንቢት ከእንግዲህ አትንገሩን፤ደስ የሚያሰኘውን ንገሩን፤የሚያማልለውን ተንብዩልን።

11. ከዚህ መንገድ ፈቀቅ በሉ፤ከጐዳናውም ራቁ፤ከእስራኤል ቅዱስ ጋርፊት ለፊት አታጋጥሙን።”

12. ስለዚህ፣ የእስራኤል ቅዱስ እንዲህ ይላል፤“ይህን ቃል ስላቃለላችሁ፣ግፍን ስለታመናችሁ፣ማታለልን ስለ ተደገፋችሁ፣

13. ስለዚህ ይህ ኀጢአት፣ተሰነጣጥቆ ሊወድቅ እንደ ደረሰ፣ሳይታሰብ ድንገት እንደሚወድቅ ረጅም ቅጥር ይሆንባችኋል።

14. ከስብርባሪዎቹም መካከል፣ለፍም መጫሪያ፣ለውሃ መጥለቂያ ገል እስከማይገኝ ድረስ፣ምንም ሳይቀር ክፉኛ እንደሚንኰታኰት፣የሸክላ ዕቃ ይደቃል።”

15. የእስራኤል ቅዱስ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“በመመለስና በማረፍ ትድናላችሁ፤በጸጥታና በመታመን ትበረታላችሁ፤እናንተ ግን ይህን አላደረጋችሁም፤

16. ደግሞም ‘አይሆንም፣ በፈረስ እንሸሻለን’ አላችሁ፤ስለዚህ ትሸሻላችሁ።ደግሞም፣ ‘በፈጣን ፈረስ እናመልጣለን’ አላችሁ፤ስለዚህ አሳዳጆቻችሁም ፈጣን ይሆናሉ።

17. በተራራ ዐናት ላይ እንደ ተተከለ ሰንደቅ ዐላማ፣በኰረብታም ላይ እንደ ቆመ ምልክት፣ሆናችሁ እስክትቀሩ ድረስበአንድ ሰው ዛቻ፣ሺህ ሰው ይሸሻል፤በአምስት ሰው፣ሁላችሁ ትሸሻላችሁ።”

18. እግዚአብሔር ግን ምሕረት ሊያደርግላችሁ ይታገሣል፤ርኅራኄም ሊያሳያችሁ ይነሣል። እግዚአብሔር የፍትሕ አምላክ ነውና፣እርሱን በመተማመን የሚጠባበቁት የተባረኩ ናቸው።

19. በኢየሩሳሌም የምትኖሩ የጽዮን ሕዝብ ሆይ፤ ከእንግዲህ ወዲህ አታለቅሱም። ለርዳታ ወደ እርሱ ስትጮኹ እንዴት ምሕረት አያደርግላችሁ ጩኸትህን እንደሰማም ፈጥኖ ይመልስልሃል።

20. ጌታ የጭንቀት እንጀራና የመከራ ውሃ ቢሰጥህም፣ አስተማሪህ ከእንግዲህ አይሰወርብህም፤ ዐይኖችህም አስተማሪህን ያያሉ።

21. ወደ ቀኝም ሆነ ወደ ግራ ዘወር ብትል ጆሮህ ከኋላህ፣ “መንገዱ ይህ ነው፤ በእርሱ ሂድ” የሚል ድምፅ ይሰማል።

22. ከዚያም በብር የተለበጡትን ጣዖቶችህንና በወርቅ የተለበዱ ምስሎችህን ታዋርዳለህ፤ “ከዚህ ወግ” ብለህም እንደ መርገም ጨርቅ ትጥላቸዋለህ።

23. በምድርም ለዘራኸው ዘር ዝናብን ይሰጥሃል፤ ከመሬትም የሚገኘው ፍሬ ምርጥና የተትረፈረፈ ይሆናል። በዚያን ቀን ከብቶችህ በትልቅ ሜዳ ላይ ይሰማራሉ።

24. የዕርሻ በሬዎችና አህዮች በመንሽና በላይዳ የተለየውን ገፈራና ድርቆሽ ይበላሉ።

25. በታላቁ የዕልቂት ቀን ምሽጎች ሲፈርሱ፣ በረጅም ተራራ ሁሉና ከፍ ባለውም ኰረብታ ሁሉ ላይ ወራጅ ወንዝ ይፈስሳል።

26. እግዚአብሔር የሕዝቡን ስብራት ሲጠግን፣ ያቈሰለውንም ሲፈውስ፣ ጨረቃ እንደ ፀሓይ ታበራለች፤ የፀሓይም ብርሃን እንደ ሰባት ቀን ብርሃን ሰባት ዕጥፍ ይደምቃል።

27. እነሆ፤ የእግዚአብሔር ስም፣ከሚነድ ቍጣ፣ ጥቅጥቅ ካለና ከሚትጐለጐል የጢስ ደመና ጋር ከሩቅ ይመጣል፤ከንፈሮቹ ቍጣን የተሞሉ ናቸው፤ምላሱም የሚባላ እሳት ነው።

28. እስትንፋሱ እንደሚጠራርግ፣እስከ ዐንገት እንደሚደርስም የውሃ ሙላት ነው፤መንግሥታትን በጥፋት ወንፊት ያበጥራቸዋል፤በሕዝቦችም መንጋጋ፣መንገድ የሚያስት ልጓም ያስገባል።

29. በሌሊት የተቀደሰ በዓል ስታከብሩእንደምትዘምሩ፣ትዘምራላችሁ፤ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣ወደ እስራኤል ዐለት፣ሰዎች ዋሽንት እየነፉ በደስታ እንደሚወጡ፣የእናንተም ልብ እንዲሁ ሐሤት ያደርጋል።

30. እግዚአብሔር በሚነድ ቍጣና በሚባላ እሳት፣በወጀብና በነጐድጓድ፣ በበረዶም ድንጋይ፣ግርማ የተሞላበትን ድምፁን ሰዎች እንዲሰሙ አድርጎ ያሰማል፤ክንዱም ስትወርድ ያሳያቸዋል።

31. የእግዚአብሔር ድምፅ አሦርን ያስደነግጣል፤በትሩም ይመታቸዋል።

32. እግዚአብሔር የሚያወርድባቸው የቅጣትበትር ሁሉ፣በከበሮና በበገና ድምፅ የታጀበ ነው፤በጦርነትም ክንዱን አሳይቶ መታቸው።

33. ከቀድሞ ጀምሮ ቶፌት የተባለ የማቃጠያስፍራ ተዘጋጅቶአል፤ለንጉሡም ተበጅቶአል፤ማንደጃ ጒድጓዱም ሰፊና ጥልቅ ነው፤በውስጡም ብዙ እሳትና ማገዶ አለ፤ የእግዚአብሔርም እስትንፋስእንደ ፈሳሽ ድኝ ያቀጣጥለዋል።