ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የውዳሴ መዝሙር

1. በዚያን ቀን እንዲህ ትላለህ፤“እግዚአብሔር ሆይ፤ቀድሞ ተቈጥተኸኝ ነበር፤አሁን ግን ከቍጣህ ተመለስህ፤ደግሞም አጽናንተኸኛልና እወድስሃለሁ።

2. እነሆ፣ እግዚአብሔር ድነቴ ነው፤እታመናለሁ፣ ደግሞም አልፈራም፤ ጌታ እግዚአብሔር ብርታቴና ዝማሬዬ ነው፤ድነቴም ሆኖአል።”

3. ከድነቴ ምንጮችውሃ በደስታ ትቀዳላችሁ።

4. በዚያን ቀን እንዲህ ትላላችሁ፤“እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ስሙንም ጥሩ፤ያደረገውንም በአሕዛብ መካከል አስታውቁ፤ስሙ ከፍ ከፍ ማለቱንም ዐውጁ።

5. ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ታላቅ ሥራ ሠርቶአልና፤ይህም ለዓለም ሁሉ ይታወቅ።

6. የጽዮን ሕዝብ ሆይ፤ እልል በሉ፤በደስታም ዘምሩ፤በመካከላችሁ ያለው የእስራኤል ቅዱስ ታላቅ ነውና።