ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 61 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የተወደደው የእግዚአብሔር ዓመት

1. የጌታ የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፤ለድኾች የምሥራች እንድሰብክ፣ እግዚአብሔር ቀብቶኛል።ልባቸው የተሰበረውን እንድጠግን፣ለምርኮኞች ነጻነትን፣ለእስረኞች መፈታትን እንዳውጅ ልኮኛል፤

2. የተወደደውን የእግዚአብሔርን ዓመት፣የአምላካችንንም የበቀል ቀን እንዳውጅ፣የሚያለቅሱትን ሁሉ እንዳጽናና ልኮኛል፤

3. በጽዮን ያዘኑትን እንዳረጋጋ፣በዐመድ ፈንታ፣የውበት አክሊል እንድደፋላቸው፣በልቅሶ ፈንታ፣የደስታ ዘይት በራሳቸው ላይ እንዳፈስላቸው፣በትካዜ መንፈስ ፈንታ፣የምስጋና መጐናጸፊያ እንድደርብላቸው ልኮኛል፤እነርሱም የክብሩ መግለጫ እንዲሆኑ፣ እግዚአብሔር የተከላቸው፣የጽድቅ ዛፎች ተብለው ይጠራሉ።

4. የጥንት ፍርስራሾችን መልሰው ይሠራሉ፤በቀድሞ ጊዜ የወደሙትን መልሰው ያቆማሉ፤ከብዙ ትውልድ በፊት የወደሙትንፍርስራሽ ከተሞች እንደ ገና ይሠራሉ።

5. መጻተኞች የበግ መንጎቻችሁን ያግዳሉ፤ባዕዳን በዕርሻችሁና በወይን ተክል ቦታችሁ ላይ ይሠሩላችኋል።

6. እናንተም የእግዚአብሔር ካህናት ተብላችሁ ትጠራላችሁ፤የአምላካችን ባሮች ትባላላችሁ፤የመንግሥታትን ሀብት ትመገባላችሁ፤በብልጽግናቸውም ትኰራላችሁ።

7. ሕዝቤ በኀፍረታቸው ፈንታ፣ዕጥፍ ይቀበላሉ፤በውርደታቸው ፈንታ፣በርስታቸው ደስ ይላቸዋል፤የምድራቸውንም ዕጥፍ ርስት ይወርሳሉ፤ዘላለማዊ ደስታም የእነርሱ ይሆናል።

8. “እኔ እግዚአብሔር ፍትሕን ስለምወድ፣ዝርፊያንና በደልን እጠላለሁ፤በታማኝነቴም የሚገባቸውን እሰጣቸዋለሁ፤ከእነርሱም ጋር የዘላለም ኪዳን አደርጋለሁ።

9. ዘሮቻቸው በመንግሥታት፣ልጆቻቸውም በሕዝቦች ዘንድ የታወቁ ይሆናሉ፤የሚያዩአቸውም ሁሉ፣ እግዚአብሔር የባረካቸው ሕዝብ እንደሆኑ ያውቃሉ።

10. በእግዚአብሔር እጅግ ደስ ይለኛል፤ነፍሴ በአምላኬ ሐሤት ታደርጋለች፤ሙሽራ ራሱን እንደሚያሳምር፣ሙሽራዪቱም በዕንቆቿ እንደምታጌጥ፣የድነትን ልብስ አልብሶኛል፤የጽድቅንም መጐናጸፊያ ደርቦልኛል።

11. ምድር ቡቃያ እንደምታበቅል፣የተክል ቦታ ችግኝ እንደሚያፈላ፣ጌታ እግዚአብሔርም በመንግሥታት ሁሉ ፊት፣ጽድቅንና ምስጋናን ያበቅላል።