ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ፍትሕ የጐደለውን ሕግ ለሚያወጡ፣ጭቈና የሞላበትን ሥርዐት ለሚደነግጉ ወዮላቸው!

2. የድኾችን መብት ለሚገፉ፣የተጨቈነውን ሕዝቤን ፍትሕ ለሚያዛቡ፣መበለቶችን ለሚበዘብዙ፣ወላጅ የሌላቸውን ልጆች ለሚመዘብሩ ወዮላቸው!

3. በምትጐበኙበት ቀን ምን ይውጣችኋል?ጥፋት ከሩቅ ሲመጣስ ምን ትሆናላችሁ?ርዳታን ለማግኘትስ ወደ ማን ትሸሻላችሁ?ሀብታችሁንስ የት ታገኙታላችሁ?

4. ከእስረኞች ጋር ከመርበትበት፣ከታረዱትም ጋር ከመጣል በቀር ምንም አይተርፋችሁም።ይህም ሁሉ ሆኖ፣ ቍጣው ገና አልበረደም።እጁም እንደ ተዘረጋ ነው።

የእግዚአብሔር ፍርድ በአሦር ላይ

5. “የቍጣዬ በትር ለሆነ፣የመቅሠፍቴም ዱላ በእጁ ላለው ለአሦራዊው ወዮለት!

6. ሀብታቸውን እንዲዘርፍ፣ ምርኮን እንዲያግበሰብስ፣እንደ መንገድ ላይ ጭቃም እንዲረግጣቸው፣አምላክ በሌለው ሕዝብ ላይ እልከዋለሁ፣በሚያስቈጣኝም ሕዝብ ላይ እሰደዋለሁ።

7. እርሱ ግን እንዲህ አላሰበም፤በልቡም ይህ አልነበረም፤ነገር ግን ዕቅዱ ለማጥፋት፣ብዙ ሕዝቦችንም ለመደምሰስ ነበር።

8. እንዲህም ይል ነበር፤‘የጦር አዛዦቼ በሙሉ ነገሥታት አይደሉምን?

9. ካልኖ እንደ ከርከሚሽ፣ሐማት እንደ አርፋድ፣ሰማርያስ እንደ ደማስቆ አይደሉምን?

10. የጣዖታትን መንግሥታት፣ምስሎቻቸው ከኢየሩሳሌምና ከሰማርያ መንግሥታት የሚበልጡትን እጄ እንደ ያዘች ሁሉ፣

11. በሰማርያና በጣዖቶቿ ያደረግሁትን፣በኢየሩሳሌምና በተቀረጹ ምስሎቿስ እንዲሁ አላደርግምን?።”

12. ጌታ በጽዮን ተራራና በኢየሩሳሌም ላይ የሚያደርገውን ሁሉ ከፈጸመ በኋላ፣ እንዲህ ይላል የአሦርን ንጉሥ ስለ ልቡ ትዕቢትና ስለ ንቀት አመለካከቱ እቀጣዋለሁ፤

13. የአሦር ንጉሥ እንዲህ ይላልና፤“ ‘ይህን ሁሉ ያደረግሁት በክንዴ ብርታት ነው፤ደግሞም በጥበቤ አስተዋይ ነኝና።የመንግሥታትን ድንበር አፈረስሁ፤ሀብታቸውን ዘረፍሁ፤ነገሥታታቸውን እንደ አንድ ኀያል ሆኜ አዋረድሁ።

14. ሰው እጁን ወደ ወፍ ጎጆ እንደሚሰድ፣እኔም እንዲሁ እጄን ወደ መንግሥታት ሀብት ሰደድሁ፤ሰዎች የተተወ ዕንቍላል እንደሚሰበስቡ፣እኔም እንዲሁ ምድርን ሁሉ ሰበሰብሁ፤ክንፉን ያራገበ የለም፤አፉንም ከፍቶ የጮኸ አልነበረም።’ ”

15. መጥረቢያ በሚቈርጥበት ሰው ላይ ይኵራራልን?መጋዝስ በሚስበው ላይ ይታበያልን?በትር በሚያነሣው ሰው ላይ ራሱን እንደሚነቀንቅ፣ዘንግም ራሱን ዕንጨት እንዳልሆነ አድርጎ እንደሚኵራራ ነው።

16. ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በፈረጠሙ ጦረኞቹ ላይ የሚያከሳ በሽታ ይልካል፤ከክብሩም በታች እንደ ነበልባል የሚንቦገቦግ እሳትይለኰሳል።

17. የእስራኤል ብርሃን እሳት፣ቅዱሱም ነበልባል ይሆናል፤በአንድ ቀንምእሾኹንና ኵርንችቱን እሳት ይበላዋል፤

18. ሕመምተኛ እየመነመነ እንደሚሞት፣የደኑን ክብርና የለማውን ዕርሻ፣ነፍስና ሥጋንም ፈጽሞ ያጠፋል።

19. በደኑ ውስጥ የሚተርፉት ዛፎች በጣም ጥቂት ናቸው፤ሕፃን ልጅ እንኳ ቈጥሮ ሊመዘግባቸው ይችላል።

የተረፉት የእስራኤል ዘሮች

20. በዚያን ቀን ከእስራኤል ዘር የተረፉት፣ከያዕቆብም ቤት የዳኑት፣ከእንግዲህ ወዲህበመታቸው ላይ አይታመኑም፤ነገር ግን በእስራኤል ቅዱስ በእግዚአብሔር ላይ፣በእውነት ይታመናሉ።

21. የተረፉት ይመለሳሉ፣ከያዕቆብ ቤት የተረፉት ወደ ኀያሉ አምላክ ይመለሳሉ።

22. እስራኤል ሆይ፤ሕዝብህ እንደ ባሕር አሸዋ ቢሆንም፣የተረፉት ብቻ ይመለሳሉ።ታላቅና ጻድቅ የሆነ ጥፋት ታውጆአል።

23. ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣የወሰነውን ጥፋት በምድር ሁሉ ላይ ያመጣል።

24. ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርእንዲህ ይላል፤“በጽዮን የምትኖሩ ሕዝቤ ሆይ፤ግብፅ እንዳደረገብህ ሁሉ በትር ያነሡብህን፣በሽመል የደበደቡህን አሦራውያንን አትፍራቸው።

25. በአንተ ላይ ያመጣሁትን ቅጣት በጥቂት ጊዜ ውስጥ አቆማለሁ፤በእነርሱም ላይ መቅሠፍቴን አመጣለሁ።”

26. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ምድያምን በሔሬብ ዐለት አካባቢ እንደመታ፣በጅራፍ ይገርፋቸዋል፤በግብፅ እንዳደረገውም ሁሉ፣በትሩን በውሆች ላይ ያነሣል።

27. በዚያን ቀን ሸክማቸው ከትከሻህ፣ቀንበራቸውም ከዐንገትህ ላይ ይነሣል፤ከውፍረትህም የተነሣቀንበሩ ይሰበራል።

28. ወደ ዐያት ይገባሉ፣በሚግሮን ያልፋሉ፤ጓዛቸውንም በማክማስ ያከማቻሉ።

29. መተላለፊያውን ዐልፈው እንዲህ ይላሉ፤“በጌባዕ ሰፍረን እናድራለን።”ራማ ደነገጠች፤የሳኦል ከተማ ጊብዓ ሸሸች።

30. የጋሊም ሴት ልጅ ሆይ፤ ጩኺላይሻ ሆይ፤ አድምምስኪን ዓናቶት ሆይ፤ መልሺላ

31. ማድሜናህ በሽሽት ላይ ነች፤የጌቢም ሕዝብ ሊደበቅ ይሮጣል።

32. በዚህ ቀን ኖብ ይደርሳሉ፤እጃቸውን በኢየሩሳሌም ኰረብታ፣በጽዮን ሴት ልጅ ተራራ ላይ በዛቻነቀነቁ።

33. እነሆ፤ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በታላቅ ኀይል ቅርንጫፎችን ይቈራርጣል፤ረጃጅም ዛፎች ይገነደሳሉ፤ከፍ ከፍ ያሉትም ይወድቃሉ።

34. ጥቅጥቅ ያለውን ደን በመጥረቢያ ይቈራርጣል፤ሊባኖስም በኀያሉ ፊት ይወድቃል።