ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ወዮ ለዳዊት ከተማ

1. ዳዊት የሰፈረብሽ ከተማ፣አርኤል፣ አርኤል ወዮልዓመት በዓመት ላይ ጨምሪ፣ዐውደ ዓመትሽም ይቀጥል።

2. ነገር ግን አርኤልን እከባለሁ፤ታለቅሳለች፤ ዋይ ዋይ ትላለች፤ለእኔም እንደ መሠዊያ ስፍራ ትሆንልኛለች።

3. በዙሪያሽ እሰፍራለሁ፤በቅጥር እከብሻለሁ፤የከበባ ዐምባም ሠርቼ አስጨንቅሻለሁ።

4. ወደ ታች ትወርጃለሽ፤ ከምድርም በታች ትናገሪያለሽ፤ንግግርሽ ከትቢያ እየተጒተመተመ ይወጣል፤ድምፅሽ እንደ መናፍስት ድምፅ ከመሬት ወደ ላይ ይመጣል፤ንግግርሽ ከትቢያ ያንሾካሹካል።

5. ነገር ግን ብዙ ጠላቶችሽ እንደ ትቢያ ብናኝ፣መንጋ ጨካኞችም በነፋስ እንደሚነጻገለባ ይሆናሉ።ድንገት ሳይታሰብም፣

6. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በነጐድጓድ፣ በምድር መናወጥና በታላቅ ድምፅ፣በዐውሎ ነፋስና በኀይለኛ ሞገድ ፈጽሞ በሚባላም የእሳት ነበልባል ይመጣል።

7. አርኤልን የሚወጋ የአሕዛብ ሁሉ መንጋ፣በእርሷና በምሽጓ ላይ አደጋ የሚጥልና የሚከባት፣እንደ ሕልምበሌሊትም እንደሚታይ ራእይ ይሆናል።

8. የተራበ ሰው በሕልሙ ሲበላ ዐድሮ፣ነገር ግን ሲነቃ ራቡ እንዳልለቀቀው፣የጠማውም ሰው በሕልሙ ሲጠጣ ዐድሮ፣ነገር ግን ሲነቃ እንደ ዛለና ጥማቱም እንዳልተወው፣የጽዮንን ተራራ የሚወጋ፣የአሕዛብ መንጋ ሁሉ እንዲሁ ይሆናል።

9. ነሁሉሉ፤ ተደነቁም፤ተጨፈኑ፤ እስከ ወዲያኛውም ታውራችሁ ቅሩ፤በወይን ጠጅ አይሁን እንጂ ስከሩ፤በሚያሰክር መጠጥ አይሁን እንጂ ተንገዳገዱ።

10. እግዚአብሔር ከባድ እንቅልፍ ጥሎባችኋል፤ዐይኖቻችሁን፣ ነቢያትን ጨፍኖባችኋል፤ራሶቻችሁን፣ ባለ ራእዮችን ሸፍኖባችኋል።

11. ይህ ሁሉ ራእይ በጥቅልል መጽሐፍ ውስጥ እንደ ታሸገ ቃል ሆኖባችኋል። ጥቅልሉንም መጽሐፍ ማንበብ ለሚችል ሰው፣ “እባክህ አንብልን” ብላችሁ ብትሰጡት፣ “ታሽጓልና አልችልም” ይላችኋል።

12. ደግሞም ጥቅልሉን መጽሐፍ ማንበብ ለማይችል ሰው፣ “እባክህን አንብልን” ብላችሁ ብትሰጡ፣ “ማንበብ አልችልም” ይላችኋል።

13. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ይህ ሕዝብ በአፉ ወደ እኔ ይቀርባል፤በከንፈሩም ያከብረኛል፤ልቡ ግን ከእኔ የራቀ ነው፤የሚያመልከኝም፣ሰው ባስተማረው ሰው ሠራሽ ሥርዐት ብቻ ነው።

14. ስለዚህ ይህን ሕዝብ በድንቅ ላይ ድንቅነገር እያደረግሁ፣ዳግመኛ አስገርመዋለሁ፤የጥበበኞች ጥበብ ይጠፋል፤የአስተዋዮችም ማስተዋል ይበናል።”

15. ሐሳባቸውን ከእግዚአብሔር ለመደበቅ፣ወደ ጥልቅ ጒድጓድ ለሚወርዱሥራቸውንም በጨለማ ለሚያከናውኑ፣“ማን ያየናል? ማንስ ያውቅብናል” ለሚሉ ወዮላቸው!

16. እናንተ ነገሮችን ትገለብጣላችሁሸክላ ሠሪውን እንደ ሸክላ ትመለከታላችሁ፤ለመሆኑ፣ ተሠሪ ሠሪውን፣“እርሱ አልሠራኝም” ይለዋልን?ሸክላ የሠራውን፣“እርሱ ምንም አያውቅም” ይለዋልን?

17. ሊባኖስ ወደ ለም ዕርሻነት ለመለወጥ፣ለም የሆነውም መሬት ወደ ዱርነት ለመለወጥ ጥቂት ጊዜ አልቀረውምን?

18. በዚያን ጊዜ ደንቈሮ የጥቅልሉን መጽሐፍ ቃል ይሰማል፤የዐይነ ስውሩም ዐይኖችከጭጋግና ከጨለማ ተላቀው ያያሉ።

19. ትሑታን በእግዚአብሔር፣ምስኪኖችም በእስራኤል ቅዱስ እንደ ገና ሐሤት ያደርጋሉ።

20. ጨካኞች እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤ፌዘኞችም በነው ይጠፋሉ፤ለክፋት ያደፈጡ ሁሉ ይወገዳሉ።

21. ሰውን በነገር በደለኛ የሚያደርጉ፣በተከሳሽ ላይ ወጥመድ የሚዘረጉ፣በሐሰት ምስክር ፍትሕን ከንጹሓን የሚቀሙ ይቈረጣሉ።

22. ስለዚህ አብርሃምን የተቤዠው እግዚአብሔርለያዕቆብ ቤት እንዲህ ይላል፤“ያዕቆብ ከእንግዲህ ወዲያ አያፍርም፤ፊቱም ከእንግዲህ አይለዋወጥም።

23. በመካከላቸው የእጄ ሥራ የሆኑ፣ልጆቻቸውን ሲያዩ፣ስሜን ይቀድሳሉ፤የያዕቆብን ቅዱስ ቅድስና ያውቃሉ፤በእስራኤልም አምላክ ፊት በፍርሀት ይቆማሉ።

24. በመንፈስ የሳቱ ያስተውላሉ፤የሚያጒረመርሙም ምክር ይቀበላሉ።”