ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በደማስቆ ላይ የተነገረ ንግር

1. ስለ ደማስቆ የተነገረ ንግር፤“እነሆ፤ ደማስቆ ከእንግዲህ ከተማነቷ ይቀራል፤የፍርስራሽ ክምር ትሆናለች።

2. የአሮኤር ከተሞች ባድማ ይሆናሉ፤የመንጎች መሰማሪያ ይሆናሉ፤የሚያስፈራቸውም የለም።

3. የተመሸገ ከተማ ከኤፍሬም፣የመንግሥት ሥልጣን ከደማስቆ ይወርዳል፤የሶርያም ቅሬታእንደ እስራኤላውያን ክብር ይሆናል”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር።

4. “በዚያን ቀን የያዕቆብ ክብር ይደበዝዛል፤የሰውነቱም ውፍረት ይሟሽሻል።

5. አጫጅ የቆመውን ሰብል ሰብስቦ፣ዛላውንም በክንዱ እንደሚያጭድ፣ይህም በራፋይም ሸለቆእንደሚለቀም ቃርሚያ ይሆናል።

6. ሆኖም የወይራ ዛፍ ሲመታ፣ሁለት ወይም ሦስት ፍሬ በቅርንጫፍ ራስ ላይ እንደሚቀር፣አራት ወይም አምስት ፍሬም ችፍግ ባለው ቅርንጫፍ ላይ እንደሚቀር፣እንዲሁ ጥቂት ቃርሚያ ይተርፋል”ይላል የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር።

7. በዚያ ቀን ሰዎች ወደ ፈጣሪያቸው ይመለከታሉ፤ዐይኖቻቸውም ወደ እስራኤል ቅዱስ ያያሉ።

8. በእጃቸውም ወደ ሠሯቸው መሠዊያዎች አይመለከቱም፤በጣቶቻቸው ላበጇቸው የዕጣን መሠዊያዎች፣ለአሼራም የአምልኮ ዐምዶችክብር አይሰጡም።

9. በዚያን ቀን በእስራኤል ልጆች ምክንያት የተተውት ጠንካራ ከተሞች ጥሻና ውድማ እንደሆኑ ሁሉ፣ እነዚህ ሁሉ ባድማ ሆናሉ።

10. አዳኝ አምላክህን ረስተሃል፤መሸሸጊያ ዐለትህንም አላስታወስህም፤ስለዚህ ምርጥ ተክል ብትተክልም፣እንግዳ ዘርንም ብትዘራ፣

11. በተከልህበት ቀን እንዲበቅል፣በዘራህበትም ማግሥት እንዲያብብ ብታደርግ እንኳ፣መከሩ በደዌና በማይሽር ሕመም ቀን፣እንዳልነበረ ይሆናል።

12. አቤት፤ የብዙ ሕዝቦች የቍጣ ድምፅእንደ ባሕር ሞገድ ይጮኻል፤አቤት፤ የሰዎች ከፍተኛ ጩኸት!እንደ ኀይለኛ ውሃ ያስገመግማል።

13. ሰዎቹ እንደ ኀይለኛ ውሃ ጩኸት ቢያስገመግሙም፣እርሱ ሲገሥጻቸው፣በኰረብታ ላይ በነፋስ እንደሚበን ትቢያ፣በዐውሎ ነፋስ ፊት እንደሚበተን ገለባ ይበተናሉ።

14. እነሆ፤ ሲመሽ ድንገተኛ ሽብር ሆነ!ከመንጋቱ በፊት ግን አንዳቸውም አልተገኙም።የዘረፉን ዕድል ፈንታ፣የበዘበዙን ዕጣ ይህ ሆነ።