ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በኢትዮጵያ ላይ የተነገረ ትንቢት

1. በኢትዮጵያ ወንዞች ዳር ለምትገኝ፣ፉር ፉር የሚሉ ክንፎች ላሉባት ምድር ወዮላት!

2. ይህችውም መልእክተኞችን በባሕር፣ከወንዞች ማዶ በደንገል ጀልባ የምትልክ ናት።እናንት ፈጣን መልእክተኞች፤ረጃጅምና ቈዳው ወደ ለሰለሰ፣ከቅርብም ከሩቅም ወደሚፈራ ሕዝብ፣ኀያልና ቋንቋው ወደማይገባ፣ወንዞች ምድሩን ወደሚከፍሉት መንግሥት፣ ሂዱ!

3. እናንት የዓለም ሕዝቦች፣በምድርም የምትኖሩ ሁሉ፣በተራሮች ላይ ምልክት ሲሰቀል ታዩታላችሁ፤መለከትም ሲነፋ ትሰሙታላችሁ።

4. እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤“ጸጥ ብዬ እቀመጣለሁ፤ከማደሪያዬም በፀሓይ ሐሩር እንደሚያ ብረቀርቅ ትኵሳት፣በመከርም ሙቀት እንደ ደመና ጠል ሆኜ እመለከታለሁ።”

5. ከመከር በፊት የአበባው ወቅት ሲያልፍ፣አበባው የጐመራ የወይን ፍሬ ሲሆን፣የወይን ሐረጉን ተቀጥላ በመግረዣ ይገርዘዋል፤የተንሰራፋውንም ቅርንጫፍ ቈራርጦ ያስወግደዋልና።

6. ሁሉም በተራራ ላይ ለሚኖሩ ነጣቂ አሞሮችለዱርም አራዊት ይተዋሉ፤አሞሮች በጋውን ሁሉ ሲበሉት ይባጃሉ፤የዱር አራዊትም ክረምቱን ሁሉ ሲበሉት ይከርማሉ።

7. በዚያን ጊዜ ለሰራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር፣ረጃጅምና ቈዳው ከለሰለሰ፣ከቅርብም ከሩቅም ከሚፈራ ሕዝብ፣ኀያልና ቋንቋው ከማይገባ፣ወንዞችም ምድሩን ከሚከፍሉት መንግሥት፣ገጸ በረከት ይመጣለታል፤ ገጸ በረከቱም የሚመጣለት የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ስም ወዳለበት ወደ ጽዮን ተራራ ነው።