ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 1 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን፣ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ፤

እምቢተኛ ሕዝብ

2. ሰማያት ሆይ፤ ስሙ! ምድር ሆይ፤ አድምጪ! እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሮአልና፤“ልጆች ወለድሁ፣ አሳደግኋቸውም፤እነርሱ ግን ዐመፁብኝ።

3. በሬ ጌታውን፣አህያ የባለቤቱን ጋጥ ያውቃል፤እስራኤል ግን አላወቀም፤ሕዝቤም አላስተዋለም።”

4. እናንተ ኀጢአተኛ ሕዝብ፣በደል የሞላበት ወገን፣የክፉ አድራጊ ዘር፣ምግባረ ብልሹ ልጆች ወዮላችሁ እግዚአብሔርን ትተዋል፤የእስራኤልን ቅዱስ አቃለዋል፤ጀርባቸውንም በእርሱ ላይ አዙረዋል።

5. ለምን ዳግመኛ ትመታላችሁ?ለምንስ በዐመፅ ትጸናላችሁ?ራሳችሁ በሙሉ ታሞአል፤ልባችሁ ሁሉ ታውኮአል።

6. ከእግር ጥፍራችሁ እስከ ራስ ጠጒራችሁጤና የላችሁም፤ቍስልና ዕባጭ እንዲሁም እዥ ብቻ ነው፤አልታጠበም፤ አልታሰረም፤በዘይትም አልለዘበም።

7. አገራችሁ ባድማ፣ከተሞቻችሁ በእሳት የተቃጠሉ ይሆናሉ፤ዐይናችሁ እያየ፣መሬታችሁ በባዕድ ይነጠቃል፤ጠፍም ይሆናል።

8. የጽዮን ሴት ልጅበወይን አትክልት ውስጥ እንዳለ ዳስ፣በዱባ ተክል ወስጥ እንደሚገኝ ጐጆ፣እንደ ተከበበም ከተማ ተተወች።

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፣እንደ ሰዶም በሆንንገሞራንም በመሰልን ነበር።

10. እናንተ የሰዶም ገዦች፤የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤እናንተ የገሞራ ሰዎች፤ የእግዚአብሔርን ሕግ አድምጡ።

11. “የመሥዋዕታችሁ ብዛትለእኔ ምኔ ነው?” ይላል እግዚአብሔር።“የሚቃጠለውን የአውራ በግናየሰቡ እንስሳትን ስብ ጠግቤአለሁ፤በበሬ፣ በበግ ጠቦትና በፍየል ደም ደስአልሰኝም።

12. በፊቴ ለመቅረብ ስትመጡ፣ይህን ሁሉ እንድታመጡ፣የመቅደሴን ደጅ እንድትረግጡ ማን ጠየቃችሁ?

13. ከንቱውን መባ አታቅርቡ፤ዕጣናችሁን እጸየፋለሁ፤የወር መባቻ በዓላችሁን፣ሰንበቶቻችሁን፣ ጉባኤያችሁንናበክፋት የተሞላውን ስብሰባችሁን መታገሥአልቻልሁም።

14. የወር መባቻችሁንና የተደነገጉ በዓሎቻችሁንነፍሴ ጠልታለች፤ሸክም ሆነውብኛል፤መታገሥም አልቻልሁም።

15. እጆቻቸሁን ለጸሎት ወደ እኔ ስትዘረጉ፣ዐይኖቼን ከእናንተ እሰውራለሁ፤አብዝታችሁ ብትጸልዩም እንኳ አልሰማችሁም፤እጆቻችሁ በደም ተበክለዋል፤

16. ታጠቡ፤ ራሳችሁንም አንጹ፤ክፉ ሥራችሁን ከፊቴ አርቁ፤ክፉ ማድረጋችሁን ተዉ፤

17. መልካም ማድረግን ተማሩ፤ፍትሕን እሹ፣የተገፉትን አጽናኑ፤አባት ለሌላቸው ቁሙላቸው፤ለመበለቶችም ተሟገቱ።

18. “ኑና እንዋቀስ”ይላል እግዚአብሔር፤“ኀጢአታችሁ እንደ ዐለላ ቢቀላእንደ በረዶ ይነጣል፤እንደ ደም ቢቀላምእንደ ባዘቶ ነጭ ይሆናል።

19. እሺ ብትሉ፣ ብትታዘዙምየምድርን በረከት ትበላላችሁ፤

20. እምቢ ብላችሁ ብታምፁ ግንሰይፍ ይበላችኋል።” የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።

21. ታማኝ የነበረችው ከተማእንዴት አመንዝራ እንደሆነች ተመልከቱቀድሞ ፍትሕ የሞላባት፣ጽድቅ የሰፈነባት ነበረች፤አሁን ግን የነፍሰ ገዳዮች ማደሪያ ሆነ

22. ብርሽ ዝጎአል፣ምርጥ የወይን ጠጅሽ ውሃ ገባው፤

23. ገዥዎችሽ ዐመፀኞችናየሌባ ግብረ ዐበሮች ናቸው፤ሁሉም ጒቦን ይወዳሉ፤እጅ መንሻንም በብርቱ ይፈልጋሉ፤አባት ለሌላቸው አይቆሙም፤የመበለቶችንም አቤቱታ አይሰሙም።

24. ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣የእስራኤል ኀያል እንዲህ ይላል፤“በባላንጣዎቼ ላይ ቍጣዬን እገልጣለሁ፤ጠላቶቼንም እበቀላለሁ።

25. እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፣ዝገትሽን ፈጽሜ አጠራለሁ፤ጒድፍሽንም ሁሉ አስወግዳለሁ።

26. ፈራጆችሽን እንደ ጥንቱ፣አማካሪዎችሽንም እንደ ቀድሞው እመልሳለሁ፤ከዚያም የጽድቅ መዲና፣የታመነች ከተማተብለሽ ትጠሪያለሽ።

27. ጽዮን በፍትሕ፣በንስሓ የሚመለሱ ነዋሪዎቿም በጽድቅ ይዋጃሉ።

28. ዐመፀኞችና ኀጢአታኞች ግን በአንድነት ይደቃሉ፤ እግዚአብሔርንም የሚተዉ ይጠፋሉ።

29. “ደስ በተሰኛችሁባቸው የአድባር ዛፎችታፍራላችሁ፤በመረጣችኋቸውም የአትክልት ቦታዎችትዋረዳላችሁ።

30. ቅጠሉ እንደ ጠወለገ ወርካ፣ውሃም እንደሌለው የአትክልት ቦታ ትሆናላችሁ።

31. ብርቱ ሰው እንደ ገለባ፣ሥራውም እንደ ብልጭታ ይሆናል፤ሁለቱም አብረው ይቃጠላሉ፤እሳቱንም የሚያጠፋው የለም።