ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 44 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የተመረጠው እስራኤል

1. “ነገር ግን አሁንም ባሪያዬ ያዕቆብ፣የመረጥሁህ እስራኤል ሆይ፣ ስማ፤

2. የፈጠረህ፣ በማሕፀን የሠራህ፣የሚረዳህ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ባሪያዬ ያዕቆብ፣የመረጥሁህ ይሹሩን ሆይ፣ አትፍራ።

3. በተጠማ ምድር ላይ ውሃ፤በደረቅ መሬት ላይ ወንዞችን አፈሳለሁና፤መንፈሴን በዘርህ፣በረከቴንም በልጅ ልጅህ ላይ አወርዳለሁ።

4. እነርሱም በለመለመ መስክ ላይ እንደ ሣር፣በወንዝ ዳር እንደ አኻያ ዛፍ ይበቅላሉ።

5. አንዱ፣ ‘እኔ የእግዚአብሔር ነኝ’ ይላል፤ሌላው ራሱን በያዕቆብ ስም ይጠራልሌላው ደግሞ በእጁ ላይ ‘የእግዚአብሔር ነኝ’ ብሎ ይጽፋል፤ራሱን በእስራኤል ስም ይጠራል።

አምላክ እግዚአብሔር ብቻ ነው

6. “የእስራኤል ንጉሥና ቤዛ እግዚአብሔር፣የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤የፊተኛውም እኔ ነኝ፤ የኋለኛውም እኔ ነኝ፤ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም።

7. እስቲ እንደ እኔ ማን አለ? ይናገር፤ሕዝቤን ከጥንት ስመሠርት ምን እንደ ነበረ፣ገና ወደ ፊት ምን እንደሚሆን፣ይናገር፤ በፊቴ ያስረዳ፤ስለሚመጣውም ነገር አስቀድሞ ይናገር።

8. አትፍሩ፤ አትደንግጡ፤ይህን አልነገርኋችሁምን? ቀድሞስ አላሳወ ቅኋችሁምን?ለዚህ እናንተ ምስክሮቼ ናችሁ። ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ አለን? ፈጽሞ!ወይም ሌላ ዐለት አለ? የለም! ማንንም አላውቅም።”

9. ጣዖት የሚሠሩ ሁሉ ከንቱዎች፣የሚሰሩባቸውም ነገሮች ዋጋ ቢስ ናቸው፤የሚናገሩላቸው ዕውሮች ናቸው፤ዕውቀት የላቸውም ያፍራሉም።

10. ለምንም የማይጠቅመውን አምላክ የሚቀርጽ፣ጣዖትን የሚያበጅስ ማነው?

11. ጣዖት የሚሠራ ሰው እንጂ ሌላ አይደለም፤እርሱና መሰሎቹም ያፍራሉ፤ሁሉም ተሰብስበው በአንድ ላይ ይቁሙ፤ይደነግጣሉ፤ ይዋረዳሉም።

12. ብረት ቀጥቃጭ መሥሪያን ይይዛል፤በከሰል ፍም ላይ ይሠራዋል፤ጣዖትን በመዶሻ ቅርጽ ይሰጠዋል፤በክንዱም ኀይል ያበጀዋል።ከዚያም ይራባል፤ ጒልበት ያጣል፤ውሃ ይጠማል፤ ይደክማል።

13. ጠራቢ በገመድ ይለካል፤በጠመኔ ንድፍ ያወጣል፤በመሮ ይቀርጸዋል፤በጸርከል ምልክት ያደርግበታል።በሰው አምሳል ይቀርጸዋል፤የሰውንም ውበት ያለብሰዋል፤በማምለኪያም ስፍራ ያስቀምጠዋል።

14. ዝግባ ይቈርጣል፤ሾላ ወይም ዋንዛ ይመርጣል፤በደን ውስጥ ካሉት ዛፎች ጋር እንዲያድግ ይተወዋል፤ወይም ጥድን ይተክላል፤ ያንንም ዝናም ያሳድገዋል።

15. ሰው ለማገዶ ይጠቀምበታል፤ከዚያም ጥቂት ወስዶ በማንደድ ይሞቀዋል፤እንጀራም ይጋግርበታል።ከዚሁ ጠርቦ አምላክ ያበጃል፤ያመልከዋል፤ጣዖትን ይሠራል፤ ወድቆም ይሰግድለታል።

16. ግማሹን ዕንጨት ያነደዋል፤በላዩ ምግቡን ያበስልበታል፤ሥጋ ጠብሶበት እስኪጠግብ ይበላል፤እሳቱን እየሞቀ እንዲህ ይላል፤“እሰይ ሞቀኝ፤ እሳቱም ይታየኛል።”

17. በቀረው ዕንጨት የጣዖት አምላኩን ይሠራበታል፤ወድቆ ይሰግድለታል፤ ያመልከዋል፤ወደ እርሱም እየጸለየ፣“አንተ አምላኬ ነህ፤ አድነኝ” ይላል።

18. ምንም አያውቁም፤ አያስተውሉም፤እንዳያዩ ዐይናቸው ተሸፍኖአል፤እንዳያስተውሉ ልባቸው ተዘግቶአል።

19. ማንም ቆም ብሎ አላሰበም፤ዕውቀት ወይም ማስተዋል ስለሌለው እንዲህ ማለት አልቻለም፤“ግማሹን በእሳት አቃጥዬዋለሁ፤በፍሙ እንጀራ ጋግሬበታለሁ፤ሥጋ ጠብሼበት በልቻለሁ፤ታዲያ፣ በቀረው እንዴት ጸያፍ ነገር እሠራለሁ?ለግንድስ መስገድ ይገባኛልን?”

20. ዐመድ ይቅማል፤ ተታላይ ልብ አስቶታል፤ራሱን ለማዳን አይችልም፤“ይህ በቀኝ እጄ ያለው ነገር ሐሰት አይደለምን?”ለማለት አልቻለም።

21. “እስራኤል ሆይ፤ ባሪያዬ ነህና፣ያዕቆብ ሆይ፤ ይህን አስብ።እኔ ሠርቼሃለሁ፤ አንተም ባሪያዬ ነህ፤እስራኤል ሆይ፤ አልረሳህም።

22. መተላለፍህን እንደ ደመና፣ኀጢአትህን እንደ ማለዳ ጭጋግ ጠርጌ አስወግጃለሁ፤ተቤዥቼሃለሁናወደ እኔ ተመለስ።”

23. ሰማያት ሆይ፤ እግዚአብሔር ይህን አድርጎአልና ዘምሩ፤የምድር ጥልቆች ሆይ፤ በደስታ ጩኹ።እናንት ተራሮች፣እናንት ደኖችና ዛፎቻችሁ ሁሉ እልል በሉ፤ እግዚአብሔር ያዕቆብን ተቤዥቶአል፣በእስራኤልም ክብሩን ገልጦአልና።

ኢየሩሳሌም የሰው መኖሪያ ትሆናለች

24. “ከማሕፀን የሠራህ፣ የተቤዠህም፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ሁሉን ነገር የፈጠርሁ፣ብቻዬን ሰማያትን የዘረጋሁ፣ምድርን ያንጣለልሁ፣እኔ እግዚአብሔር ነኝ።

25. የሐሰተኞችን ነቢያት ምልክቶች አከሽፋለሁ፤ሟርተኞችን አነሆልላለሁ፤የጥበበኞችን ጥበብ እገለባብጣለሁ፤ዕውቀታቸውንም ከንቱ አደርጋለሁ።

26. የባሪያዎቼን ቃል እፈጽማለሁ፤የመልእክተኞቼን ምክር አጸናለሁ።ኢየሩሳሌምን ‘የሰው መኖሪያ ትሆኛለሽ’፣የይሁዳ ከተሞችንም፣ ‘ይታነጻሉ’፣ፍርስራሻቸውን፣ ‘አድሳለሁ’ እላለሁ።

27. ጥልቁን ውሃ፣ ‘ደረቅ ሁን፤ወንዞችህን አደርቃለሁ’ እላለሁ።