ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 58 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

እውነተኛ ጾም

1. “በኀይል ጩኽ፤ ምንም አታስቀር፤ድምፅህን እንደ መለከት አሰማ፤ለሕዝቤ ዐመፃቸውን፣ለያዕቆብም ቤት ኀጢአታቸውን ተናገር።

2. ዕለት በዕለት ይፈልጉኛል፤መንገዴን ለማወቅ የሚጓጉ ይመስላሉ፤ትክክለኛውን ነገር እንደሚያደርግ፣የአምላኩንም ትእዛዝ እንዳልተወ ሕዝብ ሁሉ፣ተገቢ የሆነ ፍትሕ ይለምኑኛል፤እግዚአብሔር ወደ እነርሱ እንዲቀርብ የሚወዱም ይመስላሉ።

3. ‘አንተ ካልተቀበልኸው፣ስለ ምን ብለን ጾምን?አንተ ከጒዳይ ካልቈጠርኸው፣ስለ ምን ራሳችንን አዋረድን?’ ይላሉ።“ሆኖም በጾማችሁ ቀን የልባችሁን ታደርጋላችሁ፤ሠራተኞቻችሁንም ትበዘብዛላችሁ።

4. ጾማችሁ በጥልና በክርክር፣በግፍ ጡጫና በመደባደብ ይፈጸማል፤ከእንግዲህ ዛሬ እንደምትጾሙት ጾማችሁ፣ድምፃችሁ ወደ ላይ እንደሚሰማም ተስፋ አታድርጉ።

5. እኔ የመረጥሁት ጾም እንዲህ ዐይነቱን ነውን?ሰውስ ራሱን የሚያዋርደው በእንዲህ ያለው ቀን ብቻ ነውን?እንደ ደንገል ራስን ዝቅ ማድረግ ነውን?ወይስ ማቅ ለብሶ በዐመድ ላይ መንከባለል ነውን?ታዲያ ጾም ብለህ የምትጠራው ይህን ነውን? እግዚአብሔርስ የሚቀበለው እንዲህ ያለውን ቀን ነውን?

6. “እንግዲህ እኔ የመረጥሁት ጾም፣የጭቈናን ሰንሰለት እንድትበጥሱ፣የቀንበርን ገመድ እንድትፈቱ፣የተጨቈኑትን ነጻ እንድታወጡ፣ቀንበርን ሁሉ እንድትሰብሩ አይደለምን?

7. ምግብህን ለተራበ እንድታካፍለው፣ተንከራታቹን ድኻ ወደ ቤትህ እንድታስገባው፣የተራቈተውን ስታይ እንድታለብሰው፣የሥጋ ዘመድህንም ፊት እንዳትነሣው አይደለምን?

8. ይህ ከሆነ ብርሃንህ እንደ ንጋት ጮራ ይፈነጥቃል፤ፈውስህ ፈጥኖ ይደርሳል፤ጽድቅህ ቀድሞህ ይሄዳል፤ የእግዚአብሔር ክብር ደጀን ይሆንልሃል።

9. የዚያን ጊዜ ትጣራለህ፤ እግዚአብሔርም ይመልስልሃል፤ለርዳታ ትጮኻለህ፤ እርሱም፣ ‘አለሁልህ’ ይልሃል።“የጭቈና ቀንበር፣የክፋትን ንግግርና ጣት መቀሰርን ከአንተ ብታርቅ፣

10. ለተራበው ብትራራለት፣የተገፉት እንዲጠግቡ ብታደርግ፣ብርሃንህ በጨለማ ያበራል፤ሌሊትህም እንደ ቀትር ፀሓይ ይሆናል።

11. እግዚአብሔር ሁል ጊዜ ይመራሃል፤ፀሓይ ባቃጠለው ምድር ፍላጎትህን ያሟላል፤ዐጥንትህን ያበረታል፤በውሃ እንደ ረካ የአትክልት ቦታ፣እንደማይቋርጥም ምንጭ ትሆናለህ።

12. ወገኖችህ የቀድሞ ፍርስራሾችን መልሰው ይሠራሉ፤የጥንቱንም መሠረት ያቆማሉ፤አንተም፣ የተናዱ ቅጥሮችን አዳሽ፣ባለ አውራ መንገድ ከተሞችን ጠጋኝ ትባላለህ።

13. “እግሮችህ ሰንበትን እንዳይሽሩ ብታሳርፍ፣በተቀደሰው ቀኔ የልብህን ባታደርግ፣ሰንበትን ደስታ፣ የእግዚአብሔርን ቅዱስ ቀን የተከበረ ብለህ ብትጠራው፣በገዛ መንገድህ ከመሄድ፣እንደ ፈቃድህ ከማድረግና ከከንቱ ንግግር ብትቈጠብ፣

14. በዚያን ጊዜ በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፤በምድር ከፍታዎች ላይ እንድትጋልብ፣የአባትህን የያዕቆብን ርስት ጠግበህ እንድትበላ አደርግሃለሁ” የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሮአልና።