ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 60 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የጽዮን ክብር

1. “ብርሃንሽ መጥቶአልና ተነሺ አብሪ፤ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻል።

2. እነሆ፤ ጨለማ ምድርን፣ድቅድቅ ጨለማም ሕዝቦችን ይሸፍናል፤ነገር ግን እግዚአብሔር ወጥቶልሻል፤ክብሩንም ይገልጥልሻል።

3. ሕዝቦች ወደ ብርሃንሽ፣ነገሥታትም ወደ ንጋትሽ ጸዳል ይመጣሉ።

4. “ቀና በዪ፤ ዙሪያሽን ተመልከቺ፤ሁሉም ተሰብስበው ወደ አንቺ ይመጣሉ፤ወንዶች ልጆችሽ ከሩቅ፣ሴቶች ልጆችሽም በዕቅፍ ወደ አንቺ ይመጣሉ።

5. ከዚያም ታያለሽ፤ ታብረቀርቂያለሽ፤ልብሽ ይዘላል፤ በደስታም ይሞላል።በባሕሮች ያለው ሀብት ወደ አንቺ ይመጣል፤የነገሥታትም ብልጥግና የአንቺ ይሆናል።

6. የግመል መንጋ፣የምድያምና የጌፌር ግልገል ግመሎችምድርሽን ይሞላሉ፤ወርቅና ዕጣን ይዘው፣ የእግዚአብሔርን ምስጋና እያወጁ፣ሁሉም ከሳባ ይመጣሉ።

7. የቄዳር የበግ መንጋ ሁሉ ወደ አንቺ ይሰበሰባል፤የነባዮት አውራ በጎች ያገለግሉሻል።እነዚህም በመሠዊያዬ ላይ ተቀባይነት የሚኖራቸው መሥዋዕቶች ይሆናሉ፤እኔም የክብር መቅደሴን ግርማ አጐናጽፈዋለሁ።

8. “ርግቦች ወደ ጐጆአቸው እንደሚበሩ፣እንደ ደመና የሚጓዙ እነዚህ እነማን ናቸው?

9. በርግጥ ደሴቶች እኔን ተስፋ ያደርጋሉ፤እርሱ ክብሩን ስላጐናጸፈሽ፣ለእስራኤል ቅዱስ፣ ለእግዚአብሔር አምላክሽ ክብር፣ከሩቅ ወንዶች ልጆችሽን፣ከነብራቸውና ከነወርቃቸው ለማምጣት፣የተርሴስ መርከቦች ቀድመው ይወጣሉ።

10. “ባዕዳን ቅጥሮችሽን ይሠራሉ፤ነገሥታቶቻቸው ያገለግሉሻል፤በቊጣዬ ብመታሽም፣ርኅራኄዬን በፍቅር አሳይሻለሁ።

11. በሮችሽ ምንጊዜም የተከፈቱ ይሆናሉ፤ቀንም ሆነ ሌሊት ከቶ አይዘጉም፤ይህም ሰዎች የመንግሥታትን ብልጥግና ወደ አንቺ እንዲያመጡ፤ነገሥታታቸውም በድል ወደ አንቺ እንዲገቡ ነው።

12. ለአንቺ የማይገዛ ሕዝብና መንግሥት ይጠፋል፤ፈጽሞም ይደመሰሳል።

13. የመቅደሴን ቦታ ለማስጌጥ፣የሊባኖስ ክብር፣ጥዱ፣ አስታውና ባርሰነቱ በአንድነት ወደ አንቺ ይመጣሉ፤እግሬ የሚያርፍበትንም ስፍራ አከብራለሁ።

14. የአስጨናቂዎችሽ ወንዶች ልጆች እየሰገዱ ወደ አንቺ ይመጣሉ፤የናቁሽም ሁሉ እግርሽ ላይ ይደፋሉ፤ የእግዚአብሔር ከተማ፣የእስራኤል ቅዱስ ገንዘብ የሆንሽው ጽዮን ብለው ይጠሩሻል።

15. “የተተውሽና የተጠላሽ፣ማንም ሰው የማያልፍብሽ ብትሆኝም እንኳ፣እኔ የዘላለም ትምክሕት፣የትውልድም ሁሉ ደስታ አደርግሻለሁ።

16. የመንግሥታትን ወተት ትጠጫለሽ፤የነገሥታትንም ጡት ትጠቢያለሽ፤ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አዳኝሽ፣ቤዛሽም እኔ የያዕቆብ ኀያል እንደሆንሁ ታውቂያለሽ።

17. በናስ ፈንታ ወርቅ፣በብረትም ፈንታ ብር አመጣልሻለሁ።ሰላምን ገዥሽ፣ጽድቅንም አለቃሽ አደርጋለሁ።

18. ከእንግዲህ በምድርሽ ሁከት፣በጠረፎችሽም ጥፋትና መፈራረስ አይሰማም፤ነገር ግን ቅጥሮችሽን ድነት፣በሮችሽንም ምስጋና ብለሽ ትጠሪያቸዋለሽ።

19. ከእንግዲህ በቀን የፀሓይ ብርሃን አያስፈልግሽም፤በሌሊትም የጨረቃ ብርሃን አያበራልሽም፤ እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃን፣አምላክሽም ክብርሽ ይሆናልና።

20. ፀሓይሽ ከእንግዲህ አትጠልቅም፤ጨረቃሽም ብርሃን መስጠቷን አታቋርጥም፤ እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃንሽ ይሆናል፤የሐዘንሽም ቀን ያከትማል።

21. ሕዝብሽም ሁሉ ጻድቃን ይሆናሉ፤ምድሪቱንም ለዘላለም ይወርሳሉ፤ለክብሬ መግለጫ ይሆኑ ዘንድ፣የእጆቼ ሥራ፣እኔ የተከልኋቸው ቊጥቋጦች ናቸው።

22. ከአንቺ ታናሽ የሆነው ሺህ፣ከሁሉም የመጨረሻው ታናሽ ኀያል መንግሥት ይሆናል፤እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ጊዜውም ሲደርስ ይህን በፍጥነት አደርጋለሁ።”