ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 63 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

እግዚአብሔር የሚቤዥበትና የሚበቀልበት ቀን

1. ይህ ከኤዶም፣ቀይ የተነከረ መጐናጸፊያ ለብሶ ከባሶራ የሚመጣ ማን ነው?ይህ ክብርን የተጐናጸፈ፣በኀይሉ ታላቅነት እየተራመደ የሚመጣውስ ማን ነው?“በጽድቅ የምናገር፣ለማዳንም ኀይል ያለኝ እኔው ነኝ።”

2. መጐናጸፊያህ፣ ለምንበወይን መጭመቂያ ወይን እንደሚረግጡ ሰዎች ልብስ ቀላ?

3. “እኔ በመጭመቂያው ወይኑን ብቻዬን ረገጥሁ፤ከመንግሥታት ማንም ከእኔ ጋር አልነበረም፤በቍጣዬ ረገጥኋቸው፤በመዓቴም ጨፈለቅኋቸው፤ደማቸው በመጐናጸፊያዬ ላይ ተረጭቶአል፤ልብሴንም በክዬዋለሁ።

4. የበቀል ቀን በልቤ አለ፤የምቤዥበትም ዓመት ደርሶአል።

5. ተመለከትሁ፤ የሚረዳ ግን አልነበረም፤የሚያግዝ ባለመኖሩም ተገረምሁ፤ስለዚህ የገዛ ክንዴ ድነትን አመጣልኝ፤የገዛ ቊጣዬም አጸናኝ፤

6. መንግሥታትን በቍጣዬ ረጋገጥሁ፤በመዓቴም አሰከርኋቸው፤ደማቸውንም በምድር ላይ አፈሰስሁ።”

ውዳሴና ጸሎት

7. የእግዚአብሔርን ቸርነት፣ እግዚአብሔር ስላደረገልን ሁሉ፣ስለሚመሰገንበት ሥራው፣እንደ ፍቅሩና እንደ ቸርነቱ መጠን፣ለእስራኤል ቤት ያደረገውን፣አዎን፣ ስላደረገው መልካም ነገር እናገራለሁ።

8. እርሱም፣ “ርግጥ ነው፤ እነርሱ ሕዝቤ ናቸው፤የማይዋሹኝ ወንዶች ልጆቼ ናቸው” አለ።ስለዚህም አዳኝ ሆነላቸው።

9. በጭንቃቸው ሁሉ ተጨነቀ፤የፊቱም መልአክ አዳናቸው፤በፍቅሩና በምሕረቱ ዋጃቸው፤በቀደመው ዘመን ሁሉ አነሣቸው፤ተሸከማቸውም።

10. እነርሱ ግን ዐመፁ፤ቅዱስ መንፈሱንም አሳዘኑ፤ስለዚህ ተመልሶ ጠላት ሆናቸው፤እርሱ ራሱ ተዋጋቸው።

11. ከዚያም ሕዝቡ የጥንቱን ዘመን፣የሙሴንና የሕዝቡን ጊዜ እንዲህ በማለት አስታወሱ፤የበጎቹን እረኛ፣ከባሕሩ ያወጣቸው እርሱ የት አለ?ቅዱስ መንፈሱንም፣በመካከላቸው ያኖረ እርሱ የት አለ?

12. የከበረው ኀያል ክንድ፣በሙሴ ቀኝ እጅ ላይ እንዲያርፍ አደረገ፤ለራሱ የዘላለም ዝና እንዲሆንለት፣ውሆችን በፊታቸው ከፈለ።

13. ፈረስ በምድረ በዳ እንደሚያልፍ ሁሉ፣እነርሱንም በጥልቁ ውስጥ አሳልፎ መራቸው፤ስለዚህም አልተሰናከሉም፤

14. ወደ ሸለቆ እንደሚወርድ የከብት መንጋ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ዕረፍት ተሰጣቸው።ሕዝብህን በዚህ ሁኔታ የመራሃቸው፣ስምህን የከበረ ለማድረግ ነው።

15. ከተቀደሰው፣ ከተከበረውና ከፍ ካለው ዙፋንህ፣ከሰማይ ወደ ታች ተመልከት፤ኀይልህና ቅናትህ የት አለ?ገርነትህና ርኅራኄህ ከእኛ ርቀዋል።

16. አብርሃም ባያውቀን፣እስራኤልም ባያስታውሰን እንኳ፣አንተ እኮ አባታችን ነህ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አባታችን ነህ፤ከጥንትም ቢሆን ስምህ “ቤዛችን” ነው።

17. እግዚአብሔር ሆይ፤ ከመንገድህ እንድንወጣ፣ልባችንን በማደንደን ለምን እንዳንፈራህ አደረግኸን?ስለ ባሮችህ ስትል፣ስለ ርስትህ ነገዶች ስትል እባክህ ተመለስ።

18. ለጥቂት ጊዜ ሕዝብህ የተቀደሰውን ስፍራ ወርሶ ነበር፤አሁን ግን ጠላቶቻችን መቅደስህን ረገጡት።