ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 51 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የዘላለም ድነት ለጽዮን

1. “እናንት ጽድቅን የምትከታተሉ፣ እግዚአብሔርን የምትፈልጉ ስሙኝ፤ተቈርጣችሁ የወጣችሁበትን ዐለት፣ተቈፍራችሁ የወጣችሁባትንም ጒድጓድ ተመልከቱ።

2. ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፣ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሣራ ተመልከቱ፤በጠራሁት ጊዜ አንድ ራሱን ብቻ ነበር፤ባረክሁት፤ አበዛሁትም።

3. እግዚአብሔር ጽዮንን በርግጥ ያጽናናታል፤ፍርስራሾቿንም በርኅራኄ ይመለከታል፤ምድረ በዳዋን እንደ ዔድን፣በረሓዋንም እንደ እግዚአብሔር ተክል ቦታ ያደርጋል፤ተድላና ደስታ፣ምስጋናና የዝማሬ ድምፅ በእርሷ ይገኛሉ።

4. “ወገኔ ሆይ፤ አድምጠኝ፤ሕዝቤ ሆይ፤ ስማኝ፤ሕግ ከእኔ ይወጣል፤ፍርዴም ለሕዝቦች ብርሃን ይሆናል።

5. ጽድቄ በፍጥነት እየቀረበ፣ማዳኔም እየደረሰ ነው፤ክንዴም ለመንግሥታት ፍትሕን ያመጣል፤ደሴቶች ወደ እኔ ይመለከታሉ፤ክንዴንም በተስፋ ይጠብቃሉ።

6. ዐይኖቻችሁን ወደ ሰማያት አንሡ፤ወደ ታች ወደ ምድርም ተመልከቱ፤ሰማያት እንደ ጢስ በነው ይጠፋሉ፤ምድር እንደ ልብስ ታረጃለች፤ነዋሪዎቿም እንደ አሸን ፈጥነው ይረግፋሉ፤ማዳኔ ግን ለዘላለም ይኖራል፤ጽድቄም መጨረሻ የለውም።

7. “እናንት ጽድቅን የምታውቁ፣ሕጌንም በልባችሁ ያኖራችሁ ሰዎች ስሙኝ፤ሰዎች ሲዘብቱባችሁ አትፍሩ፤ሲሰድቧችሁ አትደንግጡ።

8. ብል እንደ ልብስ ይበላቸዋል፤ትል እንደ በግ ጠጒር ይውጣቸዋል፤ጽድቄ ግን ለዘላለም፣ማዳኔም ከትውልድ እስከ ትውልድ ጸንታ ትኖራለች።”

9. የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፤ተነሥ፤ ተነሥ! ኀይልን ልበስ፤እንዳለፉት ዘመናት፣በጥንት ትውልዶችም እንደሆነው ሁሉ ተነሥ።ረዓብን የቈራረጥህ፣ታላቁን ዘንዶ የወጋህ አንተ አይደለህምን?

10. የዳኑት እንዲሻገሩ ባሕሩን፣የታላቁን ጥልቅ ውሆች ያደረቅህ፣በጥልቁም ውስጥ መንገድ ያበጀህ፣አንተ አይደለህምን?

11. እግዚአብሔር የተቤዣቸው ይመለሳሉ፤በዝማሬ ወደ ጽዮን ይገባሉ፤የዘላለማዊ ደስታን አክሊል ይቀዳጃሉ፤ተድላና ደስታ ያገኛሉ፤ሐዘንና ልቅሶም ከእነርሱ ይሸሻል።

12. “የማጽናናችሁ እኔ፣ እኔው ብቻ ነኝ፤ሟች የሆኑትን ሰዎች፣እንደ ሣር የሚጠወልጉትን የሰው ልጆችለምን ትፈራለህ?

13. የፈጠረህን፣ሰማያትን የዘረጋውን፣ምድርን የመሠረተውን እግዚአብሔርን ረስተሃል፤ሊያጠፋህ ከተዘጋጀው፣ከጨቋኙ ቊጣ የተነሣ፣በየቀኑ በሽብር ትኖራለህ፤ታዲያ የጨቋኙ ቊጣ የት አለ?

14. ዐንገታቸውን የደፉ እስረኞች በፍጥነት ነጻ ይወጣሉ፤በታሰሩበትም ጒድጓድ ውስጥ አይሞቱም፤እንጀራ አያጡም።

15. ሞገዱ እንዲተም ባሕሩን የማናውጥ፣እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝና፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው።

16. ቃሌን በአፍህ አኖርሁ፤በእጄ ጥላ ጋረድሁህ፤ሰማያትን በስፍራቸው ያስቀመጥሁ፣ምድርን የመሠረትሁ፣ጽዮንንም፣ ‘አንቺ ሕዝቤ ነሽ’ ያልሁ እኔ ነኝ።

የእግዚአብሔር የቊጣ ጽዋ

17. ከእግዚአብሔር እጅ፣የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ፣ዝቃጩ እንኳ ሳይቀር፣ሰዎችን የሚያንገደግደውን ዋንጫ የጨለጥሽ፣ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ፤ተነሺ፤ ተነሺ።

18. ከወለደቻቸው ወንዶች ልጆች ሁሉ፣የመራት አንድም አልነበረም፤ካሳደገቻቸው ወንዶች ልጆች ሁሉ፣እጇን ይዞ የወሰዳት ማንም አልነበረም።

19. እነሆ፤ በጥፋት ላይ ጥፋት መጥተውብሻል፤ታዲያ ማን ያጽናናሻል?እነርሱም መፈራረስና ጥፋት፣ ራብና ሰይፍ ናቸው፤ታዲያ ማን ያስተዛዝንሽኀሀ

20. ወንዶች ልጆችሽ ዝለዋል፤በወጥመድ እንደ ተያዘ ሚዳቋ፣በየጐዳናው አደባባይ ላይ ተኝተዋል። የእግዚአብሔር ቊጣ፣የአምላክሽም ተግሣጽ ሞልቶባቸዋል።

21. ስለዚህ አንቺ የተጐዳሽ፣ያለ ወይን ጠጅ የሰከርሽ ይህን ስሚ።

22. ሕዝቡን የሚታደግ አምላክሽ፣ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ ከእጅሽ፣ያንገደገደሽን ጽዋ ወስጃለሁ፤ያንን ጽዋ፣ የቊጣዬን ዋንጫ፣ዳግም አትጠጪውም፤