ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 53 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የሰማነውን ነገር ማን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ?

2. በፊቱ እንደ ቡቃያ፣ከደረቅም መሬት እንደ ወጣ ሥር በቀለ፤የሚስብ ውበት ወይም ግርማ የለውም፤እንድንወደውም የሚያደርግ መልክ አልነበረውም።

3. በሰዎች የተናቀና የተጠላ፣የሕማም ሰውና ሥቃይ ያልተለየው ነበር።ሰዎች ፊታቸውን እንደሚያዞሩበት ዐይነት፣የተናቀ ነበር፤ እኛም አላከበርነውም።

4. በርግጥ እርሱ ደዌያችንን ወሰደ፤ሕመማችንንም ተሸከመ፤እኛ ግን በእግዚአብሔር እንደ ተመታ፣እንደ ተቀሠፈ፣ እንደ ተሠቃየም ቈጠርነው።

5. ነገር ግን እርሱ ስለ መተላለፋችን ተወጋ፤ስለ በደላችንም ደቀቀ፤በእርሱ ላይ የወደቀው ቅጣት ለእኛ ሰላም አመጣልን፤በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።

6. እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤እያንዳንዳችንም በየመንገዳችን ነጐድን፤ እግዚአብሔርም፣ የሁላችንን በደልበእርሱ ላይ ጫነው።

7. ተጨነቀ፤ ተሠቃየም፤ነገር ግን አፉን አልከፈተም፤እንደ ጠቦትም ለዕርድ ተነዳ፤በሸላቾች ፊት ዝም እንደሚል በግ፣አፉን አልከፈተም።

8. በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ስለ ሕዝቤ ኀጢአት ተመቶ፣ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ፣ከትውልዱ ማን አስተዋለ?

9. በአፉ ተንኰል ሳይገኝበት፣ምንም ወንጀል ሳይሠራ፣አሟሟቱ ከክፉዎች፣መቃብሩም ከባለጠጎች ጋር ሆነ።

10. መድቀቁና መሠቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፤ እግዚአብሔር ነፍሱን የኀጢአት መሥዋዕት ቢያደርገውም እንኳ፣ዘሩን ያያል፤ ዕድሜውም ይረዝማል፤ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።

11. ከነፍሱ ሥቃይ በኋላ፣የሕይወት ብርሃን ያያል፤ ደስም ይለዋል፤ጻድቅ ባሪያዬ በዕውቀቱ ብዙዎቹን ያጸድቃል፤መተላለፋቸውንም ይሸከማል።

12. ስለዚህ ድርሻውን ከታላላቆች ጋር እሰጠዋለሁ፤ምርኮውን ከኀያላን ጋር ይካፈላል፤እስከ ሞት ድረስ ሕይወቱን አሳልፎ በመስጠቱ፣ከክፉ አድራጊዎችም ጋር በመቈጠሩ፣የብዙዎችን ኀጢአት ተሸከመ፤ስለ ዐመፀኞችም ማለደ።