ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 48 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

እልከኛዪቱ እስራኤል

1. “የያዕቆብ ቤት ሆይ፤እናንት በእስራኤል ስም የተጠራችሁ፣ከይሁዳ ዘር የተገኛችሁ፣እናንት በእግዚአብሔር ስም የምትምሉ፣በእውነት ወይም በጽድቅ ሳይሆን፣የእስራኤልን አምላክ የምትጠሩ ይህን ስሙ!

2. እናንት የቅድስቲቱ ከተማ ነዋሪዎች ነን ብላችሁ ራሳችሁን የምትጠሩ፣በእስራኤል አምላክ የምትታመኑ፣ስሙ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር የሆነው የሚለውን አድምጡ፤

3. የቀደሙትን ነገሮች ከብዙ ዘመን በፊት ተናግሬአለሁ፤ከአፌ ወጥተዋል፤ እንዲታወቁም አድርጌአለሁ፤እኔም ድንገት ሠራሁ እነርሱም፤ ተፈጸሙ።

4. የቱን ያህል እልኸኛ እንደ ነበርህ ዐውቃለሁና፤የዐንገትህ ጅማት ብረት፣ግንባርህም ናስ ነበር።

5. ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ገና ድሮ ነገርሁህ፤ከመፈጸማቸው በፊት አስታወቅሁህ፤ ይህም፣‘ጣዖቶቼ ይህን አደረጉ፤ከዕንጨት የተቀረጸው ምስልና ከብረት የተሠራው አምላኬ ይህን ወስኖአል’እንዳትል ነው።

6. እነዚህን ነገሮች ሰምተሃል፤ ሁሉንም ተመልከታቸው፤ራስህ ትክክለኛነታቸውን አትመሰክርምን?“ከአሁን ጀምሮ አዳዲስ ነገሮችን፣የተሰወሩብህን ያላወቅሃቸውን ነገሮች እነግርሃለሁ።

7. እነርሱም የተፈጠሩት አሁን እንጂ ጥንት አይደለም፤ስለ እነርሱም ከዛሬ በፊት አልሰማህም።ስለዚህ፣ ‘አዎን፤ ስለ እነርሱ ዐውቃለሁ’ማለት አትችልም።

8. አልሰማህም ወይም አላውቅህም፤ጆሮህ ከጥንት የተከፈተ አልነበረም፤አንተ አታላይ እንደ ነበርህ፣ከልጅነትህ ጀምሮ ዐመፀኛ መባልህን ዐውቄአለሁና።

9. ስለ ስሜ ስል ቍጣዬን አዘገያለሁ፤ስለ ምስጋናዬም ስል ከአንተ እገታዋለሁ፤ይኸውም እንዳልቈርጥህ ነው።

10. እነሆ፤ እንደ ብር ባይሆንም አንጥሬሃለሁ፤በመከራ እቶን ፈትኜሃለሁ።

11. ስለ ራሴ፣ ስለ ራሴ ስል አደርጋለሁ፤ራሴን ለውርደት እንዴት አሳልፌ እሰጣለሁ?ክብሬን ለማንም አልሰጥም።

እስራኤል ነጻ ሆነች

12. “ያዕቆብ ሆይ፤የጠራሁህ እስራኤል ሆይ፤ ስማኝ፤እኔ እኔው ነኝ፤ፊተኛው እኔ ነኝ፤ ኋለኛውም እኔ ነኝ።

13. ምድርን የመሠረተች የእኔው እጅ ናት፤ሰማያትን የዘረጋችም ቀኝ እጄ ናት፤በምጠራቸው ጊዜ፣ሁሉም በአንድነት ይቆማሉ።

14. “ሁላችሁም በአንድነት ተሰብሰቡ፤ አድምጡም፤ከጣዖቶች አስቀድሞ እነዚህን የተናገረ ማን ነው? የእግዚአብሔር ምርጥ ወዳጅ የሆነ፣እርሱ በባቢሎን ላይ ያቀደውን እንዲፈጽም ያደርገዋል፤ክንዱም በባቢሎናውያን ላይ ይሆናል።

15. እኔ፣ እኔው ራሴ ተናግሬአለሁ፤በርግጥ እኔ ጠርቼዋለሁ፤አመጣዋለሁ፤ሥራውም ይከናወንለታል።

16. “ወደ እኔ ቅረቡ፤ ይህን ስሙ፤“ከመጀመሪያ ጀምሮ በስውር አልተናገርሁም፤ሲፈጸምም እኔ እዚያው ነበርሁ።”አሁንም ጌታ እግዚአብሔርና መንፈሱልከውኛል።

17. የተቤዠህ፣ የእስራኤል ቅዱስ፣ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እኔ እግዚአብሔር አምላክህ፣የሚበጅህ ምን እንደሆነ የማስተምርህ፣መሄድ በሚገባህ መንገድ የምመራህ ነኝ።

18. ትእዛዜን ሰምተህ ብቻ ቢሆን ኖሮ፣ሰላምህ እንደ ወንዝ፣ጽድቅህም እንደ ባሕር ሞገድ በሆነ ነበር።

19. ዘርህ እንደ አሸዋ፣ልጆችህ ስፍር እንደሌለው ትቢያ በሆኑ ነበር፤ስማቸው አይወገድም፤ከፊቴም አይጠፋም።

20. ከባቢሎን ውጡ፣ከባቢሎናውያንም ሽሹ!ይህን በእልልታ አስታውቁ፤ ዐውጁት፤እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ተናገሩ፤“እግዚአብሔር ባሪያውን ያዕቆብንተቤዥቶታል” በሉ።

21. በምድረ በዳ ሲመራቸው አልተጠሙም ነበር፤ውሃ ከዐለት አፈለቀላቸው፤ዐለቱን ሰነጠቀ፤ውሃውም በኀይል ፈልቆ ወጣ።

22. “ለክፉዎች ሰላም የላቸውም” ይላል እግዚአብሔር።