ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 34 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤

2. “እናንት ጠቢባን፣ ቃሌን ስሙ፤ዐዋቂዎችም አድምጡኝ።

3. ምላስ ምግብን አጣጥሞ እንደሚለይ፣ጆሮም የንግግርን ለዛ ለይቶ ያውቃል።

4. የሚበጀንን እንምረጥ፣መልካሙንም አብረን እንወቅ።

5. “ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤

6. እውነተኛ ብሆንም፣እንደ ውሸታም ተቈጥሬአለሁ፤በደል ባይኖርብኝም፣በማይፈወስ ቍስል ተመትቻለሁ።’

7. ፌዝን እንደ ውሃ የሚጠጣት፣እንደ ኢዮብ ያለ ሰው ማን ነው?

8. ከክፉ አድራጊዎች ጋር ይተባበራል፤ከኀጢአተኞችም ጋር ግንባር ይፈጥራል።

9. ‘እግዚአብሔርን ለማስደሰት መሞከር፣ለሰው አንዳች አይጠቅምም’ ብሎአልና።

10. “ስለዚህ፣ እናንተ አስተዋዮች ስሙኝ፤ክፋትን ማድረግ ከእግዚአብሔር ዘንድ፣በደልንም መፈጸም ሁሉን ከሚችል አምላክ ይራቅ።

11. ለሰው እንደ ሥራው ይመልስለታል፤እንደ አካሄዱም ይከፍለዋል።

12. በእውነት እግዚአብሔር ክፋትን አይሠራም፤ሁሉን የሚችል አምላክ ፍትሕን አያጣምምም።

13. ምድርን እንዲገዛ የሾመው አለን?የዓለምስ ሁሉ ባለቤት ያደረገው ማን ነው?

14. እርሱ መንፈሱን መልሶ ቢወስድ፣እስትንፋሱንም ወደ ራሱ ቢሰበስብ፣

15. ሥጋ ለባሽ ሁሉ በአንድነት በጠፋ፣ሰውም ወደ ዐፈር በተመለሰ ነበር።

16. “ማስተዋል ካለህ ይህን ስማ፤እኔ የምለውንም አድምጥ።

17. ፍትሕን የሚጠላ ሊያስተዳድር ይችላልን?አንተስ ጻድቁንና ኀያል የሆነውን ትኰንናለህ?

18. ነገሥታትን ‘የማትረቡ ናችሁ፣’መኳንንትንም፣ ‘ክፉዎች ናችሁ’የሚላቸው እርሱ አይደለምን?

19. ሁሉም የእጁ ሥራ ስለሆኑ፣እርሱ ለገዦች አያደላም፤ባለጠጋውንም ከድኻው አብልጦ አይመለከትም።

20. እነርሱም እኩለ ሌሊት ላይ በድንገት ይሞታሉ፤ሕዝብ ተንቀጥቅጦ ሕይወቱ ያልፋል፤ኀያላኑም የሰው እጅ ሳይነካቸው ይወገዳሉ።

21. “ዐይኖቹ የሰውን አካሄድ ይመለከታሉ፤ርምጃውንም ሁሉ ይከታተላሉ።

22. ክፉ አድራጊዎች የሚደበቁበት፣ጨለማ ስፍራ ወይም የሞት ጥላ የለም።

23. ሰው ለፍርድ ፊቱ ይቀርብ ዘንድ፣እግዚአብሔር ቀጠሮ አይዝለትም።

24. ያለ ምንም ጥያቄ ኀያላንን ያንኰታኵታል፤ሌሎችንም በቦታቸው ይሾማል።

25. እርሱ ሥራቸውን ሁሉ ስለሚያውቅ፣በሌሊት ይገለብጣቸዋል፤እነርሱም ይደቃሉ።

26. ስለ ክፋታቸውም፣በሰው ሁሉ ፊት ይቀጣቸዋል፤

27. እርሱን ከመከተል ተመልሰዋልና፤መንገዱንም ችላ ብለዋል።

28. የድኾች ልቅሶ ወደ እርሱ እንዲደርስ ሰበብ ሆኑ፤የመከረኞችን ጩኽት ሰማ።

29. እርሱ ዝም ቢል፣ ማን ሊወቅሰው ይችላል?ፊቱንስ ቢሰውር፣ ማን ሊያየው ይችላል?እርሱ ከሰውም፣ ከሕዝብም በላይ ነው፤

30. ይህም የሆነው ዐመፀኛው ሕዝቡን እንዳይገዛ፣ወጥመድም በፊታቸው እንዳይዘረጋ ነው።

31. “ሰው ለእግዚአብሔር እንዲህ ቢል፣ የተሻለ ነበር፤‘እኔ በደለኛ ነኝ፤ ከእንግዲህ ግን አልበድልም፤

32. ማየት ያልቻልሁትን አስተምረኝ፤ኀጢአት ሠርቼ እንደሆነም፣ ደግሜ አልሠራም።’

33. ታዲያ አንተ ለመናዘዝ ፈቃደኛ ሳትሆን፤እግዚአብሔር እንደ ወደድህ ይከፍልሃልን?መወሰን ያለብህ አንተ ነህ እንጂ፣ እኔ አይደለሁም፤እንግዲህ የምታውቀውን ንገረኝ።

34. “አስተዋዮች ይናገራሉ፤የሚሰሙኝም ጠቢባን እንዲህ ይሉኛል፤

35. ‘ኢዮብ ያለ ዕውቀት ይናገራል፤ቃሉም ማስተዋል ይጐድለዋል።’

36. ምነው ኢዮብ እስከ መጨረሻ በተፈተነ ኖሮ!እንደ ክፉ ሰው መልሶአልና፤

37. በኀጢአቱም ላይ ዐመፅን ጨምሮአል፤በመካከላችን ሆኖ በንቀት አጨብጭቦአል፤በእግዚአብሔርም ላይ ብዙ ተናግሮአል።”