ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ኤልፋዝ

1. ቴማናዊው ኤልፋዝም እንዲህ ሲል መለሰ፤

2. “አንድ ሰው ከአንተ ጋር ለመናገር ቢሞክር፣ ቅር ይልሃልን?ዳሩ ግን ከመናገር ማን ሊቈጠብ ይችላል?

3. እነሆ፤ አንተ ብዙዎችን ታስተምር እንደ ነበር አስብ፤የደከሙትንም እጆች ታበረታ ነበር፤

4. ቃልህ የተሰናከሉትን ያነሣ ነበር፤የሚብረከረከውንም ጒልበት ታጸና ነበር።

5. አሁን ግን መከራ አገኘህ፣ አንተም ተስፋ ቈረጥህ፤ሸነቈጠህ፤ ደነገጥህም።

6. እግዚአብሔርን መፍራት መታመኛህ፣ቀና አካሄድህም ተስፋህ አይደለምን?

7. “አሁንም አስተውል፤ ንጹሕ ሆኖ የጠፋ፣ ማን ነው?ቅኖችስ መች ተደምስሰው ያውቃሉ?

8. እኔ እንዳየሁ፣ ክፋትን የሚያርሱ፣መከራንም የሚዘሩ ያንኑ ያጭዳሉ።

9. በእግዚአብሔር እስትንፋስ ይጠፋሉ፤በቍጣውም ወላፈን ይደመሰሳሉ።

10. አንበሳ ያገሣል፤ ቍጡውም አንበሳ ይጮኻል፤የደቦል አንበሳው ጥርስ ግን ተሰብሮአል።

11. ብርቱው አንበሳ አደን በማጣት ይሞታል፤የአንበሳዪቱም ግልገሎች ይበተናሉ።

12. “ቃል በምስጢር መጣልኝ፤ጆሮዬም ሹክሹክታውን ሰማች።

13. በሚያስጨንቅ የሌሊት ሕልም ውስጥ፣ከባድ እንቅልፍም በሰዎች ላይ በወደቀ ጊዜ፣

14. ፍርሀትና መንቀጥቀጥ ያዘኝ፤ዐጥንቶቼም ሁሉ ተናወጡ።

15. መንፈስ ሽው ብሎ በፊቴ አለፈ፤የገላዬም ጠጒር ቆመ።

16. እርሱም ቆመ፣ምን እንደሆነ ግን መለየት አልቻልሁም፤አንድ ቅርጽ በዐይኔ ፊት ነበረ፤በእርጭታ ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ ሰማሁ፤

17. ‘ሥጋ ለባሽ ከእግዚአብሔር ይልቅ ጻድቅ ሊሆን ይችላልን?ሰውስ ከፈጣሪው ይልቅ ንጹሕ ሊሆን ይችላልን?

18. እግዚአብሔር በአገልጋዮቹ ላይ እምነት ካልጣለ፣መላእክቱንም በስሕተታቸው ከወቀሰ፤

19. ይልቁንስ በጭቃ ቤት የሚኖሩ፣መሠረታቸው ከዐፈር የሆነ፣ከብልም ይልቅ በቀላሉ የሚጨፈለቁ እንዴት ይሆኑ?

20. በንጋትና በምሽት መካከል ይደቃሉ፤ሳይታሰብም ለዘላለም ይጠፋሉ።