ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “አሁን ግን ኢዮብ ሆይ፣ ንግግሬን ስማ፤የምለውንም ሁሉ አድምጥ።

2. እንግዲህ አፌን እከፍታለሁ፤አንደበቴም ይናገራል።

3. ቃሌ ከቅን ልብ ይወጣል፤ከንፈሬም የማውቀውን በትክክል ይናገራል።

4. የእግዚአብሔር መንፈስ ፈጥሮኛል፤ሁሉን የሚችለውም አምላክ እስትንፋስ ሕይወት ሰጥቶኛል።

5. የምትችል ከሆነ መልስልኝ፤ተዘጋጅተህም በፊቴ ቁም።

6. በእግዚአብሔር ፊት እኔም እንዳንተው ነኝ፤የተፈጠርሁትም ደግሞ ከዐፈር ነው።

7. እኔን መፍራት የለብህም፤እጄም ሊከብድብህ አይገባም።

8. “በእርግጥ የተናገርኸውን ሰምቻለሁ፤እንዲህም ስትል አድምጫለሁ፤

9. ‘ኀጢአት የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ፤ከበደል ነጻ ነኝ፤ እድፈትም የለብኝም፤

10. እግዚአብሔር ግን ሰበብ ፈልጎብኛል፤እንደ ጠላቱም ቈጥሮኛል፤

11. እግሬን በግንድ አጣብቆአል፤እንቅስቃሴዬንም ሁሉ ይከታተላል።’

12. “ነገር ግን እግዚአብሔር ከሰው ስለሚበልጥ፣ትክክል እንዳልሆንህ እነግርሃለሁ።

13. የሰውን አቤቱታ እንደማይሰማ፣ለምን ታማርርበታለህ?

14. ሰው ባያስተውለውም፣እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ ይናገራል፤

15. ሰዎች ዐልጋቸው ላይ ተኝተው ሳሉ፣ከባድ እንቅልፍ ሲወድቅባቸው፣በሕልም፣ በሌሊትም ራእይ፣ ይናገራል።

16. በጆሯቸው ይናገራል፤በማስጠንቀቂያም ያስደነግጣቸዋል፤

17. ሰውን ከክፉ ሥራው ይመልሳል፤ከትዕቢት ይጠብቃል፤

18. ነፍሱን ከጒድጓድ፤ሕይወቱንም ከሰይፍ ጥፋት ያድናል።

19. ደግሞም ሰው ታሞ በዐልጋው ላይ ሳለ፣በዐጥንቱ የዘወትር ሥቃይ ይገሥጸዋል፤

20. ያኔም ሕይወቱ መብልን ትጠላለች፤ነፍሱም ምርጥ ምግብን ትጠየፋለች።

21. እንዳልነበረ ሆኖ ሥጋው ይመነምናል፤ተሸፍኖ የነበረው ዐጥንቱም ገጦ ይወጣል።

22. ነፍሱ ወደ ጒድጓድ፣ሕይወቱም ወደ ሞት መልእክተኞች ትቀርባለች።

23. “ሆኖም ትክክለኛውን መንገድ ለሰው ያመለክት ዘንድ፣መካከለኛም ይሆንለት ዘንድ፣ከሺህ አንድ መልአክ ቢገኝ፣

24. ለሰውየውም በመራራት፣‘ቤዛ አግኝቼለታለሁና፣ወደ ጒድጓድ እንዳይወርድ አድነው’ ቢለው፣

25. በዚህ ጊዜ ሥጋው እንደ ሕፃን ልጅ ገላ ይታደሳል፤ወደ ወጣትነቱም ዘመን ይመለሳል።

26. ወደ እግዚአብሔር ይጸልያል፤ ሞገስም ያገኛል፤የእግዚአብሔርን ፊት ያያል፤ ሐሤትም ያደርጋል፤እግዚአብሔር ወደ ጽድቅ ቦታው ይመልሰዋል።

27. ከዚያም ወደ ሰዎች መጥቶ እንዲህ ይላል፤‘ኀጢአትን ሠርቻለሁ፤ ትክክል የሆነውን አጣምሜአለሁ፤ነገር ግን የእጄን አላገኘሁም።

28. ነፍሴ ወደ ጒድጓድ እንዳትወርድ፣ታድጎአታል፤ በሕይወትም ሆኜ ብርሃን አያለሁ።’

29. “እግዚአብሔር ይህን ሁሉ፣ሁለት ሦስት ጊዜ ለሰው ያደርጋል።

30. ይኸውም የሕይወት ብርሃን ይበራለት ዘንድ፣ነፍሱን ከጒድጓድ ለመመለስ ነው።

31. “ኢዮብ ሆይ፤ ልብ ብለህ ስማኝ፤እኔ ልናገር፤ አንተ ዝም በል።

32. የምትለው ካለህ፣ መልስ ስጠኝ፤ትክክለኛነትህንም ማወቅ እፈልጋለሁና ተናገር፤

33. አለበለዚያ፣ ዝም ብለህ ስማኝ፤እኔም ጥበብን አስተምርሃለሁ።”