ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ልቤ በዚህ በኀይል ይመታል፤ከስፍራውም ዘለል ዘለል ይላል።

2. ስሙ! የድምፁን ጩኸት ስሙ፤ከአፉ የሚወጣውን ጒርምርምታ አድምጡ።

3. መብረቁን ከሰማይ ሁሉ በታች ያባርቃል፤ወደ ምድርም ዳርቻ ይልካል።

4. ከዚያም በኋላ የድምፁ ጩኸት ይመጣል፤በድምፁም ግርማ ያንጐደጒዳል፤ድምጹ በተሰማ ጊዜ፣መብረቁን የሚከለክል የለም።

5. የእግዚአብሔር ድምፅ በሚያስደንቅ ሁኔታ ያንጐደጒዳል፤እኛ የማናስተውለውንም ታላቅ ነገር ያደርጋል።

6. በረዶውን፣ ‘በምድር ላይ ውደቅ’ውሽንፍሩንም ‘ዶፍህን አውርደው’ ይላል።

7. እርሱ የፈጠራቸው ሰዎች ሁሉ ሥራውን ያውቁ ዘንድ፣እያንዳንዱ ሰው እንዳይሠራ ይገታዋል።

8. እንስሳት ይጠለላሉ፤በየዋሻቸውም ይቈያሉ።

9. ዐውሎ ነፋስ ከማደሪያው፣ብርድም ከብርቱ ነፋስ ይወጣል።

10. የእግዚአብሔር እስትንፋስ በረዶ ያስገኛል፤ሰፋፊ ውሆች ግግር በረዶ ይሆናሉ።

11. ደመናትን ርጥበት ያሸክማቸዋል፤መብረቁንም በውስጣቸው ይበትናል።

12. ያዘዘውን ለመፈጸም፣እርሱ በሚሰጠው መመሪያ፣በመላው የምድር ገጽ ላይ ይሽከረከራሉ።

13. ሰዎችን ለመቅጣት ደመና ያመጣል፤ወይም በዚሁ ምድሩን አጠጥቶ ፍቅሩን ይገልጻል።

14. “ኢዮብ ሆይ፤ ይህን ስማ፤ቆም ብለህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ዐስብ።

15. እግዚአብሔር ደመናትን እንዴት እንደሚቈጣጠር፣መብረቁንም እንዴት እንደሚያባርቅ ታውቃለህን?

16. ደመናት ሚዛን ጠብቀው እንዴት እንደሚንሳፈፉ፣በዕውቀቱ ፍጹም የሆነውን፣ የእርሱን ድንቅ ሥራ ታውቃለህን?

17. ምድር በደቡብ ነፋስ ጸጥ ባለች ጊዜ፣ከሙቀት የተነሣ በልብስህ ውስጥ የምትዝለፈለፍ ሆይ፤

18. ከቀለጠ ናስ እንደ ተሠራ መስተዋት የጠነከረውን ሰማይ ሲዘረጋ፣አብረኸው መዘርጋት ትችል ነበርን?

19. “ከጨለማችን የተነሣ እኛ ጒዳያችንን መግለጽ አንችልም፤ለእርሱ የምንለውን ንገረን።

20. እኔ መናገር እንደ ፈለግሁ ሊነገረው ይገባልን?ይዋጥ ዘንድ የሚጠይቅ ሰው አለን?

21. እንግዲህ ነፋስ ሰማያትን ካጠራ በኋላ፣እጅግ የምታበራዋን ፀሓይ፣ሊመለከት የሚችል የለም።

22. እንደ ወርቅ በሚያበራ ክብር ከሰሜን ይወጣል፤እግዚአብሔር በሚያስፈራ ግርማ ይመጣል።

23. ሁሉን የሚችል አምላክ ከአእምሯችን በላይ ነው፤ በኀይልና በፍርድ ታላቅ ነው፣ጽድቁም ብዙ ነው፤ ማንንም አይጨቍንም።

24. ስለዚህ፣ ሰዎች ይፈሩታል፤በልባቸው አስተዋዮች እንደሆኑ የሚያስቡትን አይመለከትም?”