ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 38 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

እግዚአብሔር ተናገረ

1. እግዚአብሔርም በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ሆኖ ለኢዮብ መለሰለት፤ እንዲህም አለው፤

2. “ዕውቀት በጐደለው ቃል፣ዕቅዴን የሚያጨልም ይህ ማን ነው?

3. እስቲ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤እኔ ልጠይቅህ፣አንተም መልስልኝ።

4. “ምድርን በመሠረትሁ ጊዜ አንተ የት ነበርህ?በእርግጥ የምታስተውል ከሆንህ፣ ንገረኝ።

5. ካወቅህ፣ መጠኗን ለይቶ ማን ወሰነ?በላይዋስ መለኪያ ገመድ የዘረጋ ማን ነው?

6. መሠረቶቿ ምን ላይ ተተከሉ?የማእዘን ድንጋይዋንስ ማን አቆመ?

7. ይህም የሆነው የንጋት ከዋክብት በዘመሩበት ጊዜ፣መላእክትም እልል ባሉበት ጊዜ ነበር።

8. “ባሕር ከማሕፀን በወጣ ጊዜ፣በር የዘጋበት ማን ነው?

9. ደመናውን ልብሱ፣ጨለማንም መጠቅለያው አደረግሁለት፣

10. ድንበር ወሰንሁለት፤መዝጊያና መወርወሪያውን አበጀሁለት።

11. ‘እስከዚህ ድረስ ትመጣለህ፤ ማለፍ ግን አትችልም፤የዕቡይ ማዕበልህም ገደብ ይህ ነው’ አልሁት።

12. “ከተወለድህ ጀምሮ ንጋትን አዘህ ታውቃለህን?ወይስ ወጋገን ስፍራውን እንዲይዝ አድርገሃል?

13. በዚህም የምድርን ዳርቻ ይዞ፣ክፉዎችን ከላይዋ እንዲያራግፍ አድርገሃልን?

14. ምድር ከማኅተም በታች እንዳለ የሸክላ ጭቃ ቅርጿ ይወጣል፤ቅርጿ እንደ ልብስ ቅርጽ ጐልቶ ይታያል።

15. ክፉዎች ብርሃናቸውን ተከልክለዋል፤ከፍ ያለው ክንዳቸውም ተሰብሮአል።

16. “ወደ ባሕር ምንጭ ወርደህ ታውቃለህን?ወይስ ወደ ጥልቀቱ ገብተህ በመሠረቱ ላይ ተመላልሰሃልን?

17. የሞት ደጆች ተገልጠውልሃልን?የሞትንስ ጥላ በሮች አይተሃልን?

18. የምድርን ስፋት ታውቃለህን?ይህን ሁሉ ዐውቀህ ከሆነ፣ ንገረኝ።

19. “ወደ ብርሃን መኖሪያ የሚያደርሰው መንገድ የትኛው ነው?የጨለማ መኖሪያስ ወዴት ነው?

20. ወደ ማደሪያቸው ልትወስዳቸው ትችላለህን?የመኖሪያቸውን መንገድ ታውቃለህ?

21. ያን ጊዜ ተወልደሃል! ዕድሜህ ትልቅ ነውና፣አንተስ በእርግጥ ሳታውቅ አትቀርም!

22. “ወደ በረዶው መጋዘን ገብተሃልን?የዐመዳዩንስ ማከማቻ አይተሃልን?

23. ይኸውም ለመከራ ጊዜ፣ለጦርነትና ለውጊያ ቀን ያስቀመጥሁት ነው።

24. መብረቅ ወደሚሰራጭበት ቦታ የሚያደርሰው መንገድ፣የምሥራቅም ነፋስ በምድር ላይ ወደሚበተንበት ስፍራ የሚወስደው የትኛው ነው?

25. ለዝናብ መውረጃን፣ለመብረቅም መንገድን ያበጀ ማን ነው?

26. በዚህም ማንም የማይኖርበትን ምድር፣ሰውም የሌለበትን ምድረ በዳ የሚያጠጣ፣

27. ባድማውንና በረሓውን መሬት የሚያጠግብ፣ሣርም እንዲበቅልበት የሚያደርግ ማን ነው?

28. ዝናብ አባት አለውን?የጤዛን ጠብታ ማን ወለደው?

29. በረዶ ከማን ማሕፀን ይወጣል?የሰማዩንስ ዐመዳይ ማን ይወልዳል?

30. ውሆች እንደ ድንጋይ ይጠነክራሉ፤የጥልቁ ገጽ እንደ በረዶ ይጋገራል።

31. “ፕልያዲስ የተባሉትን ውብ ከዋክብት ልትለጒም፣ወይም የኦርዮንን ማሰሪያ ልትፈታ ትችላለህን?

32. ማዛሮት የተባለውን የክዋክብት ክምችት በወቅቱ ልታወጣ፣ወይም ድብ የተባለውን ኮከብና ልጆቹን ልትመራ ትችላለህ?

33. የሰማያትን ሥርዐት ታውቃለህ?ይህንስ በምድር ላይ እንዲሠለጥን ማድረግ ትችላለህ?

34. “ድምፅህን ወደ ደመናት አንሥተህ፣ራስህን በጐርፍ ማጥለቅለቅ ትችላለህን?

35. መብረቆችን መስደድ ትችላለህ?እነርሱስ፣ ‘እነሆ፤ እዚህ አለን’ ይሉሃል?

36. ለልብ ጥበብን፣ለአእምሮም ማስተዋልን የሰጠ ማን ነው?

37. ትቢያ ሲጠጥር፣ጓሎችም እርስ በርስ ሲጣበቁ፣

38. ደመናትን ለመቍጠር ጥበብ ያለው ማን ነው?የሰማያትንስ የውሃ ገንቦ ዘንበል ማድረግ ማን ይችላል?

39. “ለአንበሳዪቱ አድነህ ግዳይ ታመጣለህን?የተራቡ የአንበሳ ግልገሎችንስ ታጠግባለህን?

40. እነርሱ በዋሻ ውስጥ ያደባሉ፤በደን ውስጥም ይጋደማሉ።