ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 40 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔርም ኢዮብን እንዲህ አለው፤

2. “ሁሉን ከሚችል አምላክ ጋር ተከራክሮ የሚረታው አለን?እግዚአብሔርን የሚወቅስ እርሱ መልስ ይስጥ!”

3. ኢዮብም ለእግዚአብሔር እንዲህ ሲል መለሰ፤

4. “እኔ ከንቱ ሰው፣ ምን እመልስልሃለሁ?እጄን በአፌ ላይ እጭናለሁ።

5. አንድ ጊዜ ተናገርሁ፤ የምመልሰው የለኝም፤ሁለተኛም ተናገርሁ፤ ከእንግዲህ አንዳች አልጨምርም።”

6. እግዚአብሔርም በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ሆኖ፣ ለኢዮብ እንዲህ ሲል ተናገረ፤

7. “እንግዲህ እንደ ወንድ ወገብህን ታጠቅ፤እኔ እጠይቅሃለሁ፤አንተም መልስልኝ።

8. “ፍርዴን ታቃልላለህን?ወይስ አንተ ጻድቅ ለመሆን እኔን ትኰንናለህ?

9. እንደ እግዚአብሔር ክንድ ያለ ክንድ አለህን?ድምፅህስ እንደ እርሱ ድምፅ ሊያንጐደጒድ ይችላልን?

10. እንግዲያስ ክብርንና ልዕልናን ተጐናጸፍ፤ግርማ ሞገስንም ተላበስ፤

11. ቍጣህን አፍስስ፤ትዕቢተኛውን ሁሉ ተመልክተህ አዋርደው፤

12. ትዕቢተኛውን ሰው ሁሉ ተመልክተህ ዝቅ አድርገው፤ክፉዎችንም በቆሙበት ስፍራ አድቅቃቸው።

13. ሁሉንም በአንድ ላይ ከዐፈር ደባልቃቸው፤ፊታቸውንም በመቃብር ውስጥ ሸፍን።

14. እኔም ቀኝ እጅህ እንደምታድንህ፣በዚያን ጊዜ አረጋግጬ እቀበላለሁ።

15. “አንተን እንደ ፈጠርሁ፣ የፈጠርሁትን፣‘ብሄሞት’ ተመልከት፤እንደ በሬ ሣር ይበላል፤

16. ብርታቱ ወገቡ ውስጥ፣ኀይሉም በሆዱ ጡንቻ ላይ ነው።

17. ጅራቱ እንደ ጥድ ዛፍ ይወዛወዛል፤የወርቹ ጅማት የተጐነጐነ ነው።

18. ዐጥንቱ እንደ ናስ ቱቦ፣እጅና እግሮቹም እንደ ብረት ዘንግ ናቸው።

19. እርሱ የእግዚአብሔር ሥራ አውራ ነው፤በሰይፍ ሊቀርበውም የሚችል ፈጣሪው ብቻ ነው።

20. ኰረብቶች ምግቡን ያበቅሉለታል፤አውሬዎችም ሁሉ በዙሪያው ይፈነጫሉ።

21. በውሃ ላይ በሚያድጉ ዕፀዋት ጥላ ሥር ይተኛል፤በረግረግ ስፍራ ደንገል መካከል ይደበቃል።

22. በውሃ ላይ የሚያድጉ ዕፀዋት በጥላቸው ይጋርዱታል፤የወንዝ አኻያ ዛፎች ይሸፍኑታል።

23. ወንዙ በኀይል ቢጐርፍም፣ አይደነግጥም፤ዮርዳኖስ እስከ አፉ ቢሞላም፣ እርሱ ተረጋግቶ ይቀመጣል።