ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “ሁሉን የሚችል አምላክ ለምን የፍርድ ቀን አይወስንም?እርሱን የሚያውቁትስ ለምን ያን ቀን እንዲያው ይጠባበቃሉ?

2. ሰዎች ድንበር ይገፋሉ፤የሰረቁትን መንጋ ያሰማራሉ።

3. የድኻ ዐደጉን አህያ ቀምተው ይሄዳሉ፤የመበለቲቱንም በሬ በመያዣነት ይወስዳሉ።

4. ችግረኛውን ከመንገድ ያስወግዳሉ፤የምድሪቱም ድኾች ይሸሸጋሉ።

5. በምድረ በዳ እንዳሉ የሜዳ አህዮች፣ድኾች ምግብ ፍለጋ ይራወጣሉ፤ከበረሓው ምድር ለልጆቻቸው ምግብ ይሻሉ።

6. ከሜዳ መኖ ይሰበስባሉ፤ከክፉዎች የወይን ቦታም ይቃርማሉ።

7. ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ያድራሉ፤በብርድም ጊዜ የሚለብሱት የላቸውም።

8. ከተራራ በሚወርድ ዝናብ በስብሰዋል፤መጠለያ አጥተው ቋጥኝ ዐቅፈዋል።

9. አባት የሌለው ልጅ ከዕቅፍ ተነጥቋል፤የድኻውም ልጅ በዕዳ ተይዞአል።

10. ዕራቍታቸውን ያለ ልብስ ይሄዳሉ፤ነዶ ይሸከማሉ፤ ግን ይራባሉ።

11. በየተረተሩ የወይራ ዘይት ያወጣሉ፤ወይን እየጠመቁ፣ ለራሳቸው ግን ይጠማሉ፤

12. የሟቾች ጣር ጩኸት ከከተማዋ ይሰማል፤የቈሰሉት ሰዎች ነፍስ ለርዳታ ይጮኻል፤እግዚአብሔር ግን ተጠያቂዎቹን ዝም ብሎአል።

13. “በብርሃን ላይ የሚያምፁ፣ጐዳናውን የማያውቁ፣በመንገዱም የማይጸኑ አሉ።

14. ቀኑ ሲመሽ፣ ነፍሰ ገዳይ ይነሣል፤ድኾችንና ችግረኞችን ይገድላል፤በሌሊትም እንደ ሌባ ያደባል፤

15. አመንዝራ በዐይኑ ድንግዝግዝታን ይጠባበቃል፤‘ማንም አያየኝም’ ብሎ ያስባል፤ፊቱንም ይሸፍናል።

16. በጨለማ፣ ቤት ሰርስረው ይገባሉ፤በቀን ግን ይሸሸጋሉ፤ብርሃንንም አይፈልጉም።

17. ድቅድቅ ጨለማ ለሁላቸው እንደ ንጋት ነው፤አሸባሪውን ጨለማ ይወዳጃሉ።

18. “ይሁን እንጂ፣ በውሃ ላይ የሚኵረፈረፍ ዐረፋ ናቸው፤የወይን ቦታው ሰው የማይደርስበት፣ርስታቸው ርጉም ነው።

19. ድርቅና ሙቀት የቀለጠውን በረዶ ከቦታው እንደሚያስወግድ፣ሲኦልም ኀጢአተኞችን ትነጥቃለች።

20. የተሸከመቻቸው ማሕፀን ትረሳቸዋለች፤ትል ይቦጠቡጣቸዋል፤ክፉዎች እንደ ዛፍ ይሰበራሉ፤የሚያስታውሳቸውም የለም።

21. የማትወልደውን መካኒቱን ይቦጠቡጣሉ፤ለመበለቲቱም አይራሩም።

22. ነገር ግን እግዚአብሔር ብርቱዎችን በኀይሉ ጐትቶ ይጥላል፤ቢደላደሉም የሕይወት ዋስትና የላቸውም።

23. ያለ ሥጋት እንዲኖሩ ትቶአቸው ይሆናል፤ዐይኖቹ ግን በመንገዳቸው ላይ ናቸው።

24. ለጥቂት ጊዜ ከፍ ከፍ ይላሉ፤ ሆኖም ይጠፋሉ፤ዝቅ ዝቅ ብለው፤ እንደ ሌሎቹ ይከማቻሉ።እንደ እህል ራስም ይታጨዳሉ።

25. “ይህ እንዲህ ካልሆነማ፣ የሚያስተባብለኝ ማን ነው?ቃሌን ከንቱ የሚያደርገውስ ማን ነው?”