ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዮብ 17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. መንፈሴ ደክሞአል፣ዘመኔ አጥሮአል፤መቃብርም ተዘጋጅቶልኛል።

2. አላጋጮች ከበውኛል፤ትኵረቴም ትንኰሳቸው ላይ ነው።

3. “እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ተያዥ ሁነኝ፤ከአንተ ሌላ ዋስ የሚሆነኝ ማን አለ?

4. እንዳያስተውሉ ልባቸውን ይዘሃል፤ስለዚህ ድል አትሰጣቸውም።

5. ለጥቅም ሲል ወዳጁን የሚያወግዝ፣የልጆቹ ዐይን ይታወራል።

6. “እግዚአብሔር ለሰው ሁሉ መተረቻ፣ፊቱ ላይ የሚተፋበት ሰውም አደረገኝ።

7. ዐይኔ ከሐዘን የተነሣ ፈዘዘ፤መላ አካሌም እንደ ጥላ ሆነ።

8. ቅኖች በዚህ ነገር ይደነግጣሉ፤ንጹሓንም በዐመፀኞች ላይ ይነሣሉ።

9. ጻድቃን ግን በያዙት መንገድ ይጸናሉ፤ንጹሕ እጅ ያላቸውም እየበረቱ ይሄዳሉ።

10. “ነገር ግን እናንተ ሁላችሁ፣ እስቲ ተመልሳችሁ እንደ ገና ሞክሩ!ከመካከላችሁ አንድም ጠቢብ አላገኝም።

11. ዕድሜዬ አለቀ፤ ዕቅዴም ከሸፈ፤የልቤም ሐሳብ ከንቱ ሆነ።

12. እነዚህ ሰዎች ሌሊቱን ወደ ቀን ይለውጣሉ፤ጨልሞም እያዩ፣ ‘ብርሃን ቀርቦአል’ ይላሉ።

13. ተስፋ የማደርገው ቤት መቃብር ብቻ ከሆነ፣መኝታዬንም በጨለማ ካነጠፍሁ፣

14. መበስበስን፣ ‘አንተ አባቴ ነህ፤’ትልንም፣ ‘አንቺ እናቴ’ ወይም ‘እኅቴ ነሽ’ ካልሁ፣

15. ታዲያ፣ የእኔ ተስፋ ወዴት ነው?ተስፋዬን የሚያይልኝስ ማን ነው?

16. ወደ ሞት ደጅ ይወርዳልን?አብረንስ ወደ ትቢያ እንሄዳለንን?”