ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 50 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ስለ ባቢሎን የተነገረ መልእክት

1. እግዚአብሔር ስለ ባቢሎንና ስለ ባቢሎናውያን ምድር፣ በነቢዩ ኤርምያስ በኩል የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

2. “በሕዝቦች መካከል ተናገሩ፤ አስታውቁም፤ሰንደቅ ዐላማ አንሡ፤ ዐውጁ፤አንዳች ሳታስቀሩ፣ እንዲህ በሉ፤‘ባቢሎን ትያዛለች፤ቤል ይዋረዳል፤ሜሮዳክ በሽብር ይሞላል፤ጣዖቶቿ ይዋረዳሉ፤አማልክቷም ይሸበራሉ።’

3. ከሰሜን አንድ መንግሥት መጥቶ ይወጋታል፤ምድሯንም ባድማ ያደርጋል፤የሚኖርባትም አይገኝም፤ሰዎችና እንስሳትም ሸሽተው ይሄዳሉ።

4. “በዚያ ዘመን፣ በዚያ ጊዜም፤”ይላል እግዚአብሔር፤“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ በአንድነት ይመጣሉ፤አምላካቸውንም እግዚአብሔርን በመፈለግ እያለቀሱ ይመጣሉ።

5. ወደ ጽዮን የሚወስደውን መንገድ ይጠይቃሉ፤ፊታቸውንም ወደዚያ ያቀናሉ።መጥተውም ከቶ በማይረሳ፣በዘላለም ቃል ኪዳን፣ ከእግዚአብሔር ጋር ይጣበቃሉ።

6. “ሕዝቤ የጠፉ በጎች ሆነዋል፤እረኞቻቸው አሳቷቸው፤በተራሮችም ላይ እንዲቅበዘበዙ አደረጓቸው፤በተራራና በኰረብታ ላይ ተንከራተቱ፤ማደሪያቸውንም ረሱ።

7. ያገኛቸው ሁሉ ይውጣቸዋል፤ጠላቶቻቸውም፣ ‘እኛ በደለኞች አይደለንም፤እነርሱ የአባቶቻቸውን ተስፋ እግዚአብሔርን፣እውነተኛ ማደሪያቸው የሆነውን እግዚአብሔርን በድለዋል’ አሉ።

8. “ከባቢሎን ሽሹ፤የባቢሎናውያንን ምድር ልቀቁ፤መንጋ እንደሚመራ የፍየል አውራ ሁኑ።

9. የታላላቅ መንግሥታትን ማኅበር፣ከሰሜን በባቢሎን ላይ አስነሣለሁ፤እነርሱም በእርሷ ላይ ይሰለፋሉ፤መጥተውም ይይዟታል።ቀስቶቻቸው ባዶ እጃቸውን እንደ ማይመለሱ፣እንደ ሥልጡን ተዋጊዎች ናቸው።

10. የባቢሎን ምድር ትዘረፋለች፤የሚዘርፏትም ሁሉ እስኪበቃቸው ይመዘብሩአታል፤”ይላል እግዚአብሔር።

11. “እናንተ ርስቴን የበዘበዛችሁ ሆይ፤ደስ ስላላችሁና ሐሤትም ስላደረጋችሁ፣በመስክ እንዳለች ጊደር ስለ ፈነጫችሁ፤እንደ ድንጒላ ፈረስ ስለ አሽካካችሁ፤

12. እናታችሁ እጅግ ታፍራለች፤የወለደቻችሁም ትዋረዳለች።እርሷም ምድረ በዳ፣ ደረቅ ምድርና በረሓ፣ከመንግሥታትም ሁሉ ያነሰች ትሆናለች።

13. ከእግዚአብሔር ቍጣ የተነሣ ባድማ ትሆናለች እንጂ፣የሚኖርባት አይገኝም፤በቍስሎችዋም ሁሉ ምክንያት፣በባቢሎን የሚያልፍ ሁሉ ይገረማል፤ ያፌዝባታልም።

14. “እናንተ ቀስት የምትገትሩ ሁሉ፣በባቢሎን ዙሪያ ተሰለፉ፤አንዳች ሳታስቀሩ ፍላጾችን ስደዱባት፤ በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአት ሠርታለችና።

15. ከየአቅጣጫው ጩኹባት፤እጇን ትሰጣለች፤ ምሽጓም ይወድቃል፤ቅጥሮቿ ይፈርሳሉ።ይህ የእግዚአብሔር በቀል ነውና፣እርሷን ተበቀሏት፤በሌሎቹ ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

16. ከባቢሎን ዘር የሚዘራውን፣በመከር ጊዜ ማጭድ የጨበጠውንም ዐጫጅ አጥፉት፤ከአጥፊው ሰይፍ የተነሣ፣እያንዳንዱ ወደ ገዛ ሕዝቡ ይመለስ፤ወደ ገዛ ምድሩም ይሽሽ።

17. “እስራኤል አንበሶች ያሳደዱት፣የተበተነ መንጋ ነው፤መጀመሪያ የአሦር ንጉሥ፣ቦጫጭቆ በላው፤በኋላም የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር፣አጥንቱን ቈረጣጠመው።”

18. ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የአሦርን ንጉሥ እንደ ቀጣሁት ሁሉ፣የባቢሎንን ንጉሥና ምድሩን እቀጣለሁ።

19. እስራኤልንም ወደ መሰማሪያው እመልሰዋለሁ፤በቀርሜሎስና በባሳን ላይ ይሰማራል፤በኤፍሬም ተራሮችና በገለዓድም ላይ፣እስኪጠግብ ይመገባል።

20. በእነዚያ ጊዜያት፣ በዚያ ዘመን፣”ይላል እግዚአብሔር፤“የእስራኤል በደል ይፈለጋል፤አንዳችም አይገኝም፤የይሁዳም ኀጢአት ይፈለጋል፤ከቶም የለም፤እንዲተርፉ ያደረግኋቸውን ትሩፋን እምራለሁና።

21. “የምራታይምን ምድር፣የፋቁድ ነዋሪዎችንም፣አሳዷቸው፤ ግደሏቸው፤ ፈጽማችሁም አጥፏቸው፤”ይላል እግዚአብሔር፤“ያዘዝኋችሁንም ሁሉ አድርጉ።

22. በምድሪቱ የጦርነት ውካታ፣የታላቅ ጥፋት ድምፅ ተሰማ።

23. የምድር ሁሉ መዶሻ፣እንዴት ተሰበረ! እንዴትስ ደቀቀ!በሕዝቦች መካከል፣ባቢሎን እንዴት ባድማ ሆነች!

24. ባቢሎን ሆይ፤ ወጥመድ ዘርግቼልሻለሁ፤አንቺም ሳታውቂ ተይዘሻል፤ እግዚአብሔርን ተገዳድረሻልና፣ተገኘሽ፤ ተያዝሽም።

25. እግዚአብሔር የመሣሪያ ግምጃ ቤቱን ከፍቶአል፤የቍጣውን የጦር ዕቃ አውጥቶአል፤የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፣በባቢሎናውያን ምድር ሥራ አለውና።

26. ከሩቅ መጥታችሁ በእርሷ ላይ ውጡ፤ጐተራዎቿን አፈራርሱ፤እንደ እህል ክምር ከምሯት፤ፈጽማችሁ አጥፏት፤ምኗም አይቅር።

27. ወይፈኖቿን ሁሉ ዕረዱ፤ወደ መታረጃም ይውረዱ!የሚቀጡበት ጊዜ፣ቀናቸው ደርሶአልና ወዮላቸው!

28. እግዚአብሔር አምላካችን የተበቀለውን፣ስለ ቤተ መቅደሱ የተበቀለውን በቀል፣ከባቢሎን የመጡ ኰብላዮችና ስደተኞች፣በጽዮን የሚናገሩትን ስሟቸው።

29. “ቀስት የሚገትሩትን፣ቀስተኞችን ሁሉ በባቢሎን ላይ ጥሩ፤አንድም ሰው እንዳያመልጥ፣ዙሪያውን ሁሉ መሽጉ፤የእስራኤልን ቅዱስ፣ እግዚአብሔርን አቃላለችና፣እንደ ሥራዋ መጠን መልሱላት፤በሌሎች ላይ እንዳደረገችውም አድርጉባት።

30. ስለዚህ ወንዶች ወጣቶቿ በየአደባባዩ ይረግፋሉ፤በዚያ ቀን ወታደሮቿ ሁሉ ይወድቃሉ፤”ይላል እግዚአብሔር፤

31. “አንተ ትዕቢተኛ፤ እነሆ፣ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ፤”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤“የምትቀጣበት ጊዜ፣ቀንህ ደርሶአልና።

32. ትዕቢተኛው ይሰናከላል፤ ይወድቃልም፤የሚያነሣውም የለም፤በዙሪያው ያሉትን ሁሉ የሚበላ እሳት፣በከተሞቹ ውስጥ አስነሣለሁ።”

33. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“የእስራኤል ሕዝብና የይሁዳ ሕዝብ፣በአንድነት ተጨቍነዋል፤የማረኳቸውም ሁሉ አጥብቀው ይዘዋቸዋል፤ይለቅቋቸውም ዘንድ እንቢ ብለዋል።

34. ነገር ግን ቤዛቸው ብርቱ ነው፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ለምድራቸው ዕረፍትን ለመስጠት፤ተግቶ ይሟገትላቸዋል፤በባቢሎን የሚኖሩትን ግን ዕረፍት ይነሣቸዋል።

35. “ሰይፍ በባቢሎናውያን ላይ መጣ!”ይላል እግዚአብሔር፤“በባቢሎን ነዋሪዎች ላይ፤በባለ ሥልጣኖቿና በጥበበኞቿም ላይ ተመዘዘ!

36. ሰይፍ በሐሰተኞች ነቢያቷ ላይ መጣ!እነርሱም ሞኞች ይሆናሉ፤ሰይፍ በጦረኞቿ ላይ ተመዘዘ፤እነርሱም ይሸበራሉ።

37. ሰይፍ በፈረሰኞቿና በሠረገሎቿ ላይ፣በመካከሏ ባሉት ባዕዳን ወታደሮች ሁሉ ላይ መጣ!እነርሱም እንደ ሴቶች ይሆናሉ፤ሰይፍ በሀብት ንብረቷ ላይ መጣ!ለዝርፊያም ይሆናሉ።

38. ድርቅ በውሆቿ ላይ መጣ!እነሆ፤ ይደርቃሉ፤ምድሪቱ በፍርሀት በሚሸበሩ አማልክት፣በጣዖትም ብዛት ተሞልታለችና።

39. “ስለዚህ የምድረ በዳ አራዊትና የጅብ መኖሪያ፣የጒጒትም ማደሪያ ትሆናለች፤ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አይኖርባትም፤ከትውልድ እስከ ትውልድም የሚቀመጥባት አይገኝም።

40. እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን፤በዙሪያቸውም የነበሩትን ከተሞች ያለ ነዋሪ እንዳስቀራቸው”ይላል እግዚአብሔር፤“እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፣የሚቀመጥባትም አይገኝም።

41. “እነሆ፤ ሰራዊት ከሰሜን ይመጣል፤አንድ ኀያል መንግሥትና ብዙ ነገሥታት፣ከምድር ዳርቻ ተነሣሥተዋል።

42. ቀስትና ጦር ይዘዋል፤ጨካኞች ናቸው፤ ምሕረትም አያደርጉም፤በፈረሳቸው እየጋለቡ ሲመጡ፣ድምፃቸው እንደ ባሕር ሞገድ ይተማል፤ ያስገመግማል።አንቺ የባቢሎን ሴት ልጅ ሆይ፤ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ተዋጊዎች ይመጡብሻል።

43. የባቢሎን ንጉሥ ስለ እነርሱ ሰማ፤እጆቹም በድን ሆኑ፤ጭንቀት ይዞታል፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት ታሟል።

44. አንበሳ ከዮርዳኖስ ደኖች ድንገት ወጥቶ፣ወደ ግጦሽ ሜዳ ብቅ እንደሚል፣እኔም ባቢሎንን ሳይታሰብ ከምድሯ አባርራታለሁ፤የመረጥሁትንም በእርሷ ላይ እሾማለሁ፤እንደ እኔ ያለ ማን ነው? ማንስ ሊገዳደረኝ ይችላል?የትኛውስ እረኛ ሊቋቋመኝ ይችላል?

45. ስለዚህ እግዚአብሔር በባቢሎን ላይ ያቀደውን፣በባቢሎናውያንም ምድር ላይ ያሰበውን ስሙ፤ከመንጋው ታናናሹ ተጐትቶ ይወሰዳል፤በእነርሱም ምክንያት መሰማሪያቸውን ፈጽሞ ያጠፋል።

46. በባቢሎን ውድቀት ድምፅ ትናወጣለች፤ጩኸቷም በሕዝቦች መካከል ያስተጋባል።