ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በሸክላ ሠሪው ቤት

1. ከእግዚአብሔር ወደ ኤርምያስ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦

2. “ተነሥተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ በዚያ መልእክቴን እሰጥሃለሁ።”

3. እኔም ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ወረድሁ፤ ሸክላውንም በመንኵ ራኩር ላይ ይሠራ ነበር።

4. ከጭቃ ይሠራው የነበረውም ሸክላ በእጁ ላይ ተበላሸ፤ ሸክላ ሠሪውም በሚፈልገው ሌላ ቅርጽ መልሶ አበጀው።

5. የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤

6. “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ሸክላ ሠሪው እንደሚሠራው፣ እኔ በእናንተ ላይ መሥራት አይቻለኝምን?” ይላል እግዚአብሔር፤ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ጭቃው በሸክላ ሠሪው እጅ እንዳለ፣ እናንተም እንዲሁ በእጄ ውስጥ ናችሁ።

7. አንድ ሕዝብ ወይም መንግሥት እንዲነቀል፣ እንዲፈርስና እንዲጠፋ በተናገርሁ ጊዜ፣

8. ያስጠነቀቅሁት ሕዝብ ከክፋቱ ቢመለስ፣ እኔ ላደርስበት ያሰብሁትን ክፉ ነገር እተዋለሁ።

9. በሌላም ጊዜ አንድን ሕዝብ ወይም መንግሥት አንጸውና እተክለው ዘንድ ተናግሬ፣

10. በፊቴ ክፉ ነገር ቢያደርግና ባይታዘዘኝ፣ አደርግለታለሁ ብዬ ያሰብሁትን መልካም ነገር አስቀርበታለሁ።

11. “አሁንም እንግዲህ ለይሁዳ ሕዝብና በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ እንዲህ በላቸው፤ ‘እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “እነሆ፤ ጥፋትን እያዘጋጀሁላችሁ ነው፤ ክፋትንም እየጠነሰስሁላችሁ ነው። ስለዚህ ሁላችሁ ከክፉ መንገዳችሁ ተመለሱ፤ መንገዳችሁንና ተግባራችሁን አቅኑ።” ’

12. እነርሱ ግን፣ ‘በከንቱ አትድከም፤ ባቀድነው እንገፋበታለን፤ እያንዳንዳችንም የክፉ ልባችንን እልኸኝነት እንከተላለን’ ይላሉ።”

13. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እስቲ አሕዛብን፣‘እንዲህ ዐይነት ነገር በመካከላችሁ ተሰምቶ ያውቃል?’ ብላችሁ ጠይቁ።ድንግሊቱ እስራኤል፣እጅግ ክፉ ነገር አድርጋለች።

14. የሊባኖስ ተራራ ድንጋያማ ተረተር፣በረዶ ተለይቶት ያውቃልን?ከጋራው የሚወርደውስ ቀዝቃዛ ውሃ፤መፍሰሱን ያቋርጣልን?

15. ሕዝቤ ግን ረስቶኛል፤ለማይረቡ ነገሮች ዐጥኖአል፣በራሱ መንገድ፣በቀደሞው ጐዳና ተሰናክሎአል፤በሻካራው መሄጃ፣ባልቀናውም ጥርጊያ መንገድ ሄዶአል።

16. ምድራቸው ባድማ፣ለዘላለም መሣለቂያ ይሆናል፤በዚያ የሚያልፍ ሁሉ ይደነቃል፤በመገረምም ራሱን ይነቀንቃል።

17. ከምሥራቅ እንደሚወጣ ነፋስ፣በጠላቶቻቸው ፊት እበትናቸዋለሁ፤በመጥፊያቸው ቀን፣ጀርባዬን እንጂ ፊቴን አላሳያቸውም።”

18. እነርሱም፣ “ሕግ ከካህናት፣ ምክር ከጠቢባን፣ ቃልም ከነቢያት ስለማይታጣ ኑና በኤርምያስ ላይ እንማከር፤ ኑ፤ በአንደበታችን እናጥቃው፣ እርሱ የሚናገረውንም ሁሉ አንስማ” አሉ።

19. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስማኝ፤ባላንጣዎቼ የሚሉትን አድምጥ።

20. የመልካም ተግባር ወሮታው ክፉ ነውን?እነርሱ ግን ጒድጓድ ቈፈሩልኝ፤ቍጣህን ከእነርሱ እንድትመልስ፣በፊትህ ቆሜ፣ስለ እነርሱ እንደ ተናገርሁ አስብ።

21. ስለዚህ ልጆቻቸውን ለራብ፣ለሰይፍም ስለት አሳልፈህ ስጥ፤ሚስቶቻቸው የወላድ መካን፣ መበለትም ይሁኑ፤ወንዶቻቸው በሞት ይቀሠፉ፤ጒልማሶቻቸው በጦር ሜዳ ለሰይፍ ይዳረጉ።

22. ሊይዙኝ ጒድጓድ ስለ ቈፈሩ፣ለእግሮቼም በስውር ወጥመድ ስለ ዘረጉ፣በድንገት ወራሪ ስታመጣባቸው፣ከቤታቸው ጩኸት ይሰማ።

23. አንተ ግን እግዚአብሔር ሆይ፤ሊገድሉኝ ያሴሩብኝን ሴራ ሁሉ ታውቃለህ፤በደላቸውን ይቅር አትበል፤ኀጢአታቸውንም ከፊትህ አትደምስስ፤በፊትህ ወድቀው የተጣሉ ይሁኑ፤በቍጣህም ጊዜ አትማራቸው።