ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 30 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

አጉር የተናገራቸው ምሳሌዎች

1. የያቄ ልጅ የአጉር ቃል ይህ ነው፤ይህ ሰው ለኢቲኤል፣ለኢቲኤልና ለኡካል ተናገረ፤

2. “እኔ ከሰው ሁሉ ይልቅ ጅል ነኝ፤ሰው ያለው ማስተዋል የለኝም።

3. ጥበብን አልተማርሁም፤ስለ ቅዱሱም ዕውቀት የለኝም።

4. ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው?ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው?ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው?የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው?ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል?የምታውቅ ከሆነ እስቲ ንገረኝ!

5. “የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንከን የለበትም፤እርሱ ለሚታመኑበት ሁሉ ጋሻቸው ነው።

6. በእርሱ ቃል ላይ አንዳች አትጨምር፤አለዚያ ይዘልፍሃል፤ ሐሰተኛም ያደርግሃል።

7. “እግዚአብሔር ሆይ፤ ሁለት ነገር እለምንሃለሁ፤እነዚህንም ከመሞቴ በፊት አትከልክለኝ፤

8. ሐሰትንና ሐሰት መናገርን ከእኔ አርቅልኝ፤ድኽነትንም ሆነ ብልጽግናን አትስጠኝ፤ብቻ የዕለት እንጀራዬን ስጠኝ።

9. ያለዚያ ግን ያለ ልክ እጠግብና እክድሃለሁ፤‘እግዚአብሔር ማን ነው?’ እላለሁ፤ወይም ድኻ እሆንና እሰርቃለሁ፤የአምላኬንም ስም አሰድባለሁ።

10. “አገልጋይን በጌታው ፊት በክፉ አታንሣው፤አለዚያ ይረግምህና ጒዳት ያገኝሃል።

11. “አባቱን የሚረግም፣እናቱን የማይባርክ ትውልድ አለ፤

12. ራሳቸውን ንጹሓን አድርገው የሚቈጥሩ፣ሆኖም ከርኵሰታቸው ያልነጹ አሉ፤

13. ዐይናቸው ትዕቢተኛ የሆነ፣ አስተያያቸው ንቀት የሞላበት፣

14. ድኾችን ከምድር፣ችግረኞችንም ከሰው ዘር መካከል ለማጥፋት፣ጥርሳቸው ሰይፍ የሆነ፣መንጋጋቸውም ካራ የሆነ አሉ።

15. “አልቅት ሁለት ሴት ልጆች አሉት፤‘ስጡን! ስጡን!’ እያሉ ይጮኻሉ፤“ፈጽሞ የማይጠግቡ ሦስት ነገሮች አሉ፤‘በቃኝን’ ከቶ የማያውቁ አራት ናቸው፤

16. እነርሱም መቃብር፣ መካን ማሕፀን፣ውሃ ጠጥታ የማትረካ ምድር፣‘በቃኝ’ የማይል እሳት ናቸው።

17. “በአባት ላይ የምታፌዝ ዐይን፣የእናትንም ትእዛዝ የምትንቅ፣የሸለቆ ቊራዎች ይጐጠጒጧታል፤ጆፌ አሞሮችም ይበሏታል።

18. “እጅግ የሚያስደንቁኝ ሦስት ነገሮች አሉ፤የማላስተውላቸውም አራት ናቸው፤

19. የንስር መንገድ በሰማይ፣የእባብ መንገድ በቋጥኝ፣የመርከብ መንገድ በባሕር፣የሰውም መንገድ ከሴት ልጅ ጋር ናቸው።

20. “የአመንዝራዪቱ መንገድ ይህ ነው፤በልታ አፏን በማበስ፣‘ምንም የሠራሁት ጥፋት የለም’ ትላለች።

21. “ምድር በሦስት ነገር ትናወጣለች፤እንዲያውም መሸከም የማትችላቸው አራት ነገሮች ናቸው፤

22. ባሪያ ሲነግሥ፣ሰነፍ እንጀራ ሲጠግብ፣

23. የተጠላች ሴት ባል ስታገባ፣ሴት ባሪያ በእመቤቷ እግር ስትተካ።

24. “በምድር ላይ አራት ነገሮች ትንንሽ ናቸው፤ሆኖም እጅግ ጠቢባን ናቸው፤

25. ጒንዳኖች ደካማ ፍጡራን ናቸው፤ሆኖም ምግባቸውን በበጋ ያከማቻሉ።

26. ሽኮኮዎች ዐቅመ ደካማ ናቸው፤ሆኖም መኖሪያቸውን በቋጥኞች መካከል ይሠራሉ፤

27. አንበጦች ንጉሥ የላቸውም፤ሆኖም ቅደም ተከተል ይዘው ይጓዛሉ፤

28. እንሽላሊት በእጅ ትያዛለች፤ሆኖም በቤተ መንግሥት ትገኛለች።

29. “አረማመዳቸው ግርማዊ የሆነ ሦስት ነገሮች አሉ፤እንዲያውም በሞገስ የሚጐማለሉ አራት ናቸው፤

30. ከአራዊት መካከል ኀይለኛ የሆነው፣ከምንም ነገር ፊት ግንባሩን የማያጥፈው አንበሳ፤

31. ጐርደድ ጐርደድ የሚል አውራ ዶሮ፣ አውራ ፍየል፣እንዲሁም በሰራዊቱ የታጀበ ንጉሥ ናቸው።

32. ተላላ ሆነህ ራስህን ከፍ ከፍ ካደረግህ፣ወይም ክፉ ነገር ካቀድህ፣እጅህን በአፍህ ላይ አድርግ።

33. ወተት ሲናጥ ቅቤ እንደሚወጣው፣አፍንጫን ሲያሹት እንደሚደማ፣ቊጣን ማነሣሣትም ጥልን ይፈጥራል።