ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 28 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ክፉ ሰው ማንም ሳያሳድደው ይሸሻል፤ጻድቅ ግን እንደ አንበሳ ልበ ሙሉ ነው።

2. አገር ስታምፅ፣ ገዦቿ ይበዛሉ፤አስተዋይና ዐዋቂ ሰው ግን ሥርዐትን ያሰፍናል።

3. ድኾችን የሚያስጨንቅ ሰው፣ሰብል እንደሚያጠፋ ኀይለኛ ዝናብ ነው።

4. ሕግን የሚተዉ ክፉዎችን ያወድሳሉ፤ሕግን የሚጠብቁ ግን ይቋቋሟቸዋል።

5. ክፉዎች ፍትሕን አያስተውሉም፤ እግዚአብሔርን የሚሹ ግን ሙሉ በሙሉ ያውቁታል።

6. በአካሄዱ ነውር የሌለበት ድኻ፣መንገዱ ጠማማ ከሆነ ባለጠጋ ይሻላል።

7. ሕግን የሚጠብቅ አስተዋይ ልጅ ነው፤ከሆዳሞች ጋር ጓደኛ የሚሆን ግን አባቱን ያዋርዳል።

8. በከፍተኛ ወለድ ሀብቱን የሚያካብት፣ለድኻ ለሚራራ፣ ለሌላው ሰው ያከማችለታል።

9. ሕግን ላለመስማት ጆሮውን የሚደፍን፣ጸሎቱ እንኳ አስጸያፊ ነው።

10. ቅኖችን በክፉ መንገድ የሚመራ፣በቈፈረው ጒድጓድ ይገባል፤ንጹሓን ግን መልካም ነገርን ይወርሳሉ።

11. ባለጠጋ ራሱን ጠቢብ አድርጎ ይቈጥር ይሆናል፤አስተዋይ የሆነ ድኻ ግን መርምሮ ያውቀዋል።

12. ጻድቃን ድል ሲነሡ ታላቅ ደስታ ይሆናል፤ክፉዎች ሥልጣን ሲይዙ ግን ሕዝብ ይሸሸጋል።

13. ኀጢአቱን የሚሰውር አይለማም፤የሚናዘዝና የሚተወው ግን ምሕረትን ያገኛል።

14. እግዚአብሔርን ዘወትር የሚፈራ ሰው ቡሩክ ነው፤ልቡን የሚያደነድን ግን መከራ ላይ ይወድቃል።

15. ታዳጊ በሌለው ሕዝብ ላይ የተሾመ ጨካኝ ገዥ፣እንደሚያገሣ አንበሳ ወይም ተንደንድሮ እንደሚይዝ ድብ ነው።

16. ጨካኝ ገዥ ማመዛዘን ይጐድለዋል፤ያላግባብ የሚገኝን ጥቅም የሚጸየፍ ግን ዕድሜው ይረዝማል።

17. የሰው ደም ያለበት ሰው፣ዕድሜ ልኩን ሲቅበዘበዝ ይኖራል፤ማንም ሰው አይርዳው።

18. አካሄዱ ነቀፋ የሌለበት ሰው ክፉ አያገኘውም፤መንገዱ ጠማማ የሆነ ግን ድንገት ይወድቃል።

19. መሬቱን የሚያርስ የተትረፈረፈ ምግብ ያገኛል፤ከንቱ ተስፋን ይዞ የሚጓዝ ግን ድኽነትን ይወርሳል።

20. ታማኝ ሰው እጅግ ይባረካል፤ሀብት ለማግኘት የሚጣደፍ ግን ከቅጣት አያመልጥም።

21. አድልዎ ማድረግ መልካም አይደለም፤ሰው ግን ለቊራሽ እንጀራ ሲል በደል ይፈጽማል።

22. ስስታም ሀብት ለማከማቸት ይስገበገባል፤ድኽነት እንደሚጠብቀውም አያውቅም።

23. ሸንጋይ አንደበት ካለው ይልቅ፣ሰውን የሚገሥጽ ውሎ ዐድሮ ይወደዳል።

24. ከአባት ከእናቱ ሰርቆ፣“ይህ ጥፋት አይደለም” የሚል የአጥፊ ተባባሪ ነው።

25. ስስታም ሰው ጠብን ያነሣሣል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን ይባረካል።

26. በራሱ የሚታመን ተላላ ነው፤በጥበብ የሚመላለስ ግን ክፉ አያገኘውም።

27. ለድኾች የሚሰጥ አይቸገርም፤አይቶአቸው እንዳላየ የሚሆን ግን ብዙ ርግማን ይደርስበታል።