ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ምሳሌ 7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ከአመንዝራ ሴት መራቅ

1. ልጄ ሆይ፤ ቃሌን ጠብቅ፤ትእዛዜንም በውስጥህ አኑር።

2. ትእዛዜን ጠብቅ፤ በሕይወት ትኖራለህ፤ትምህርቴንም እንደ ዐይንህ ብሌን ተንከባከበው።

3. በጣትህ ላይ እሰረው፤በልብህ ጽላት ላይ ጻፈው።

4. ጥበብን፣ “እኅቴ ነሽ” በላት፤ማስተዋልንም፣ “ዘመዴ ነህ” በለው፤

5. ከአመንዝራ ሴት፣በአንደበቷም ከምታታልል ዘልዛላ ሴት ይጠብቁሃል።

6. በቤቴ መስኮት፣በዐይነ ርግቡ ወደ ውጭ ተመለከትሁ።

7. ማስተዋል የጐደለውን ወጣት፣ብስለት ከሌላቸው መካከል አየሁት፤ከጎልማሶችም መካከል ለየሁት።

8. የቤቷን አቅጣጫ ይዞ፣በቤቷ ማእዘን አጠገብ ባለው መንገድ ያልፍ ነበር፤

9. ቀኑ መሸትሸት ሲል፣በውድቅት ሌሊት፣ በጽኑ ጨለማ።

10. ከዚያም አንዲት ሴት ልታገኘው ወጣች፤እንደ ዝሙት አዳሪ ለብሳ፣ ለማሳሳት ታጥቃ።

11. ጯኺና ማን አለብኝ ባይ ናት፤እግሮቿ አርፈው ቤት አይቀመጡም፤

12. አንዴ በመንገድ፣ አንዴ በአደባባይ፤በየማእዘኑም ታደባለች።

13. አፈፍ አድርጋ ይዛ ሳመችው፤ኀፍረቷንም ጥላ እንዲህ አለችው፤

14. “በቤቴ የኅብረት መሥዋዕት ማቅረብ ነበረብኝ፤ዛሬ ስእለቴን ፈጸምሁ፤

15. ስለዚህ አንተን ለማግኘት ወጣሁ፤ፈልጌህ ነበር፤ ይኸው አገኘሁህ።

16. ዐልጋዬን ከግብፅ የመጣ፣ጌጠኛ በፍታ አልብሼዋለሁ።

17. ዐልጋዬን፣የከርቤ፣ የዓልሙንና የቀረፋ ሽቱ አርከፍክፌበታለሁ።

18. ና፤ እስኪነጋ በጥልቅ ፍቅር እንርካ፤በፍቅር ራሳችንን እናስደስት።

19. ባሌ እቤት የለም፤ሩቅ አገር ሄዷል።

20. በገንዘብ የተሞላ ቦርሳ ወስዷል፤ጨረቃዋ ሙሉ እስክትሆን አይመለስም።”

21. በሚያግባቡ ቃላት አሳተችው፤በለሰለሰ አንደበቷ አታለለችው።

22. ለዕርድ እንደሚነዳ በሬ፣ወደ ወጥመድ እንደሚገባ አጋዘን፣ሳያንገራግር ተከተላት፤

23. ፍላጻ ጒበቱን እስኪወጋው ድረስ፣ሕይወቱን እንደሚያሳጣው ሳያውቅ፣በራ ወደ ወጥመድ እንደምትገባ ወፍ ሆነ።

24. ልጆቼ ሆይ፤ አሁንም አድምጡኝ፤የምለውንም ልብ ብላችሁ ስሙኝ።

25. ልባችሁን ወደ መንገዷ አታዘንብሉ፤ወደ ስሕተት ጐዳናዋም አትግቡ።

26. አዋርዳ የጣለቻቸው ብዙ ናቸው፤የገደለቻቸውም ስፍር ቊጥር የላቸውም።

27. ቤቷ ወደ ሲኦል የሚወስድ፣ወደ ሞት ማደሪያም የሚያወርድ ጐዳና ነው።