ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 74 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ስለ መቅደሱ መፍረስ የቀረበ ጸሎት

የአሳፍ ትምህርት

1. አምላክ ሆይ፤ ለዘላለም የጣልኸን ለምንድን ነው?በማሰማሪያህ ባሉ በጎችህስ ላይ ቍጣህ ለምን ነደደ?

2. ጥንት ገንዘብህ ያደረግሃትን ጉባኤ፣የዋጀሃትን የርስትህን ነገድ፣መኖሪያህ ያደረግሃትን የጽዮን ተራራ አስብ።

3. እርምጃህን ለዘላለሙ ባድማ ወደ ሆነው አቅና፤ጠላት በመቅደስህ ውስጥ ያለውን ሁሉ አበላሽቶአል።

4. ጠላቶችህ በመገናኛ ስፍራህ መካከል ደነፉ፤አርማቸውንም ምልክት አድርገው በዚያ አቆሙ።

5. በጫካ መካከል ዛፎችን ለመቍረጥ፣መጥረቢያ የሚያነሣ ሰው መሰሉ።

6. በእደ ጥበብ ያጌጠውን ሥራ ሁሉ፣በመጥረቢያና በመዶሻ ሰባበሩት።

7. መቅደስህን አቃጥለው አወደሙት፤የስምህንም ማደሪያ አረከሱ።

8. በልባቸውም፣ “ፈጽሞ እንጨቍናቸዋለን” አሉ፤እግዚአብሔር በምድሪቱ ላይ የተመለከበትን ስፍራ ሁሉ አቃጠሉ።

9. የምናየው ምልክት የለም፤ከእንግዲህ የሚነሣ አንድም ነቢይ የለም፤ይህ እስከ መቼ እንደሚቀጥል የሚያውቅ በእኛ ዘንድ የለም።

10. አምላክ ሆይ፤ ጠላት የሚያሾፈው እስከ መቼ ነው?ባላንጣስ ለዘላለም በስምህ ያላግጣልን?

11. እጅህን ለምን ትሰበስባለህ?ቀኝ እጅህን ለምን በብብትህ ሥር ታቆያለህ?

12. አምላክ ሆይ፤ አንተ ከጥንት ጀምሮ ንጉሤ ነህ፤በምድር ላይ ማዳንን አደረግህ።

13. ባሕርን በኀይልህ የከፈልህ አንተ ነህ፤የባሕሩንም አውሬ ራሶች በውሃ ውስጥ ቀጠቀጥህ።

14. የሌዋታንን ራሶች አደቀቅህ፤ለምድረ በዳ ፍጥረታትም ምግብ አድርገህ የሰጠሃቸው፣

15. ምንጮችንና ፈሳሾችን ያፈለቅህ አንተ ነህ፤ሳያቋርጡ የሚፈሱትንም ወንዞች አደረቅህ።

16. ቀኑ የአንተ ነው፤ ሌሊቱም የአንተ ነው፤ጨረቃንና ፀሓይን አንተ አጸናሃቸው።

17. የምድርን ዳርቻ ሁሉ የወሰንህ አንተ ነህ፤በጋውንም ክረምቱንም አንተ ሠራህ።

18. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላት እንዴት እንደሚያሾፍ፣ከንቱ ሕዝብም ስምህን እንዴት እንዳቃለለ አስብ።

19. የርግብህን ነፍስ አሳልፈህ ለዱር አራዊት አትስጥ፤የችግረኞች ሕዝብህን ሕይወት ለዘላለሙ አትርሳ።

20. ኪዳንህን አስብ፤የዐመፅ መናኸሪያ በምድሪቱ ጨለማ ስፍራዎች ሞልተዋልና።

21. የተጨቈኑት አፍረው አይመለሱ፤ድኾችና ችግረኞች ስምህን ያመስግኑ።

22. አምላክ ሆይ፤ ተነሥ፤ ለዐላማህ ተሟገት፤ከንቱ ሰው ቀኑን ሙሉ እንደሚያላግጥብህ አስብ።

23. የባላጋራዎችህን ድንፋታ፣ዘወትር የሚነሣውን የጠላቶችህን ፉከራ አትርሳ።