ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 136 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ምስጋና በቅብብሎሽ መዝሙር

1. እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

2. የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

3. የጌቶችን ጌታ አመሰግኑ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

4. እርሱ ብቻውን ታላላቅ ታምራትን የሚያደርግ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

5. ሰማያትን በብልኀት የሠራ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

6. ምድርን በውሃ ላይ የዘረጋ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።

7. ታላላቅ ብርሃናትን የሠራ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

8. ፀሓይ በቀን እንዲሠለጥን ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

9. ጨረቃና ከዋክብት በሌሊት እንዲሠለጥኑ ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

10. የግብፅን በኵር የመታ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

11. እስራኤልን ከመካከላቸው ያወጣ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

12. በኀያል እጅና በተዘረጋች ክንድ ይህን ያደረገ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

13. የኤርትራን ባሕር ለሁለት የከፈለ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

14. እስራኤልን በመካከሉ ያሳለፈ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

15. ፈርዖንንና ሰራዊቱን በኤርትራ ባሕር ያሰጠመ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

16. ሕዝቡን በምድረ በዳ የመራ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

17. ታላላቅ ነገሥታትን የመታ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

18. ኀያላን ነገሥታትን የገደለ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

19. የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን የገደለ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

20. የባሳንን ንጉሥ ዐግን የገደለ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

21. ምድራቸውን ርስት አድርጎ የሰጠ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

22. ለባሪያው ለእስራኤል ርስት አድርጎ የሰጠ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

23. በውርደታችን ጊዜ ያሰበን፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

24. ከጠላቶቻችን እጅ ያዳነን፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

25. ለፍጡር ሁሉ ምግብን የሚሰጥ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና፤

26. የሰማይን አምላክ አመስግኑ፤ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።