ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 102 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በክፉ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ባዘነና ልመናውን በእግዚአብሔር ፊት ባፈሰሰ ጊዜ፣ የተጨነቀ ሰው ጸሎት

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤ጩኸቴም ወደ አንተ ይድረስ።

2. በመከራዬ ቀን፣ ፊትህን ከእኔ አትሰውር፤ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል፤በጠራሁህ ቀን ፈጥነህ መልስልኝ።

3. ዘመኔ እንደ ጢስ ተኖ አልቆአልና፤ዐጥንቶቼም እንደ ማንደጃ ግለዋል።

4. ልቤ ዋግ እንደ መታው ሣር ደርቆአል፤እህል መብላትም ዘንግቻለሁ።

5. ከጩኸቴ ድምፅ የተነሣ፣ዐጥንቴ ከቈዳዬ ጋር ተጣበቀ።

6. የምድረ በዳ እርኩም መሰልሁ፤በፍርስራሽ መካከል እንዳለ ጒጒት ሆንሁ።

7. ያለ እንቅልፍ አድራለሁ፤በቤቴ ጒልላት ላይ እንዳለ ብቸኛ ወፍ ሆንሁ።

8. ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ ይዘልፉኛል፤የሚያክፋፉኝም ስሜን እንደ ርግማን ቈጥረውታል።

9. ዐመድ እንደ እህል ቅሜአለሁና፤መጠጤንም ከእንባ ጋር ቀላቅያለሁ።

10. ከቍጣህና ከመዓትህ የተነሣ፣ወደ ላይ አንሥተኸኝ የነበርሁትን መልሰህ ጣልኸኝ።

11. ዘመኖቼ እንደ ምሽት ጥላ ናቸው፤እኔም እንደ ሣር ደርቄአለሁ።

12. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ለዘላለም በዙፋንህ ተቀምጠሃል፤ስምህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

13. ትነሣለህ፤ ጽዮንንም በርኅራኄ ዐይን ታያለህ፤ለእርሷ በጎነትህን የምታሳይበት ዘመን ነውና፤የተወሰነውም ጊዜ ደርሶአል።

14. አገልጋዮችህ በድንጋዮቿ ደስ ይሰኛሉ፤ለዐፈሯም ይሳሳሉ።

15. ሕዝቦች የእግዚአብሔርን ስም፣የምድርም ነገሥታት ሁሉ ክብርህን ይፈራሉ።

16. እግዚአብሔር ጽዮንን መልሶ ይሠራታልና፤በክብሩም ይገለጣል።

17. እርሱ ወደ ችግረኞች ጸሎት ይመለከታል፤ልመናቸውንም አይንቅም።

18. ወደ ፊት የሚፈጠር ሕዝብ እግዚአብሔርን ያወድስ ዘንድ፣ይህ ለመጪው ትውልድ እንዲህ ተብሎ ይጻፍ፤

19. “እግዚአብሔር በከፍታ ላይ ካለው መቅደሱ ወደ ታች ተመልክቶአልና፤ከሰማይም ሆኖ ምድርን አይቶአል፤

20. ይኸውም የእስረኞችን ጩኸት ይሰማ ዘንድ፣ሞት የተፈረደባቸውንም ያድን ዘንድ ነው።”

21. ስለዚህ የእግዚአብሔር ስም በጽዮን፣ምስጋናውም በኢየሩሳሌም ይታወጃል፤

22. ይህም፣ ሕዝቦችና መንግሥታት፣ እግዚአብሔርን ለማምለክ በአንድነት ሲሰበሰቡ ይሆናል።

23. ብርታቴን መንገድ ላይ ቀጨው፤ዕድሜዬንም ባጭሩ አስቀረው።

24. እኔም እንዲህ አልሁ፤“አምላኬ ሆይ፤ በዘመኔ እኵሌታ አትውሰደኝ፤ዘመናትህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራሉ።

25. አንተ ከጥንት ምድርን መሠረትህ፤ሰማያትም የእጆችህ ሥራ ናቸው።

26. እነርሱ ይጠፋሉ፤ አንተ ግን ጸንተህ ትኖራለህ፤ሁላቸው እንደ ልብስ ያረጃሉ፤እንደ መጐናጸፊያም ትለውጣቸዋለህ፤እነርሱም ወዲያ ይጣላሉ።

27. አንተ ግን ያው አንተ ነህ፤ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም።

28. የአገልጋዮችህ ልጆች ተደላድለው ይኖራሉ፤ዘራቸውም በፊትህ ጸንቶ ይኖራል።