ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 109 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በጠላት ላይ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር

1. የምስጋናዬ ምንጭ የሆንህ አምላክ ሆይ፤ ዝም አትበል፤

2. ክፉዎችና አታላዮች፣አፋቸውን ከፍተውብኛልና፤በውሸተኛ አንደበት ተናግረውብኛል።

3. በጥላቻ ቃል ከበውኛል፤ያለ ምክንያትም ጥቃት አድርሰውብኛል።

4. ስወዳቸው ይወነጅሉኛል፤እኔ ግን እጸልያለሁ።

5. በበጎ ፈንታ ክፋትን፣በወደድኋቸው ፈንታ ጥላቻን ይመልሱልኛል።

6. ክፉ ሰው በላዩ ሹም፤ከሳሽም በቀኙ ይቁም።

7. ፍርድ ፊት ሲቆም በደለኛ ሆኖ ይገኝ፤ጸሎቱም ለፍርድ ትሁንበት።

8. ዕድሜው ይጠር፤ሹመቱንም ሌላ ይውሰደው።

9. ልጆቹ ድኻ አደጎች ይሁኑ፤ሚስቱም መበለት ትሁን።

10. ልጆቹ ይንከራተቱ፤ ለማኞችም ይሁኑ፤ከፈረሰው ቤታቸውም ይሰደዱ።

11. ያለውን ሁሉ ዕዳ ጠያቂ ይውረሰው፤የድካሙንም ዋጋ ባዕዳን ይቀሙት።

12. ማንም ሰው ምሕረት አያድርግለት፤ለድኻ አደግ ልጆቹም የሚራራ አይኑር።

13. ዘሩ ተለይቶ ይጥፋ፤ስማቸውም በሚቀጥለው ትውልድ ይደምሰስ።

14. የአባቶቹ በደል በእግዚአብሔር ፊት ይታሰብ፤የእናቱም ኀጢአት አይደምሰስ።

15. መታሰቢያቸውን ከምድር ያጠፉ ዘንድ፣ኀጢአታቸው ሁል ጊዜ በእግዚአብሔር ፊት ይኑር፤

16. ችግረኛውንና ምስኪኑን፣ ልቡም የቈሰለውን፣እስከ ሞት አሳደደ እንጂ፣ምሕረት ያደርግ ዘንድ አላሰበምና።

17. መራገምን ወደደ፤ ወደ እርሱም መጣች፤በመባረክ ደስ አልተሰኘም፤በረከትም ከእርሱ ራቀች።

18. መርገምን እንደ ልብስ ለበሳት፤እርሷም እንደ ውሃ ወደ ውስጥ ሰውነቱ፤እንደ ዘይትም ወደ ዐጥንቱ ዘለቀች።

19. ገላውን እንደሚሸፍንበት ልብስ፣ዘወትር እንደሚታጠቀውም መቀነት ትሁነው።

20. እግዚአብሔር ለሚወነጅሉኝ ሰዎች፣በነፍሴም ላይ ክፉ ለሚናገሩ የሚከፍላቸው ይኸው ይሁን።

21. አንተ ግን ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤ስለ ስምህ በበጎ ተመልከተኝ፤ምሕረትህም መልካም ናትና አድነኝ።

22. እኔ ድኻና ችግረኛ ነኝና፤ልቤም በውስጤ ቈስሎአልና።

23. እንደ ምሽት ጥላ ከእይታ ተሰውሬአለሁ፤እንደ አንበጣም ረግፌአለሁ።

24. ከጾም የተነሣ ጒልበቴ ዛለ፤ሰውነቴም ከስቶ ዐመድ ለበሰ።

25. ለመሣለቂያ ሆንሁላቸው፤ሲያዩኝም ራሳቸውን ይነቀንቃሉ።

26. እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ርዳኝ፤እንደ ምሕረትህም አድነኝ።

27. እግዚአብሔር ሆይ፤ እጅህ ይህን እንዳደረገች፣አንተም ይህን እንደ ፈጸምህ ይወቁ።

28. እነርሱ ይራገማሉ፤ አንተ ግን ትባርካለህ፤በሚነሡበት ጊዜ ይዋረዳሉ፤ባሪያህ ግን ሐሤት ያደርጋል።

29. የሚወነጅሉኝ ውርደትን ይከናነቡ፤ዕፍረትንም እንደ ሸማ ይልበሱ።

30. እግዚአብሔርን በአንደበቴ እጅግ አመሰግናለሁ፤በታላቅ ሕዝብም መካከል አወድሰዋለሁ።

31. በነፍሱ ላይ ከሚፈርዱት ያድነው ዘንድ፣እርሱ በችግረኛው ቀኝ በኩል ይቆማልና።