ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 55 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

በስደት ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ የዳዊት ትምህርት

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን ስማ፤ልመናዬን ቸል አትበል፤

2. ወደ እኔ ተመልከት፤ መልስልኝም።በውስጤ ታውኬአለሁ፤ ተናውጬአለሁም፤

3. በጠላት ድምፅ ተሸበርሁ፤በክፉዎች ድንፋታ ደነገጥሁ፤መከራ አምጥተውብኛልና፤በቍጣም ተነሣሥተው ጠላት ሆነውብኛል።

4. ልቤ በውስጤ ተጨነቀብኝ፤የሞት ድንጋጤም በላዬ መጣ።

5. ፍርሀትና እንቅጥቃጤ መጣብኝ፤ሽብርም ዋጠኝ።

6. እኔም እንዲህ አልሁ፤ “ምነው የርግብ ክንፍ በኖረኝ!በርሬ በሄድሁና ባረፍሁ ነበር፤

7. እነሆ፤ ኰብልዬ በራቅሁ፣በምድረ በዳም በሰነበትሁ ነበር፤ ሴላ

8. ከዐውሎ ነፋስና ከውሽንፍር ሸሽቼ፣ወደ መጠለያዬ ፈጥኜ በደረስሁ ነበር።”

9. ጌታ ሆይ፤ ግፍንና ሁከትን በከተማዪቱ ውስጥ አይቼአለሁና፣ግራ አጋባቸው፤ ቋንቋቸውንም ደበላልቅ።

10. ቀንና ሌሊት ቅጥሯ ላይ ወጥተው ይዞሯታል፤ተንኰልና መከራ በውስጧ አለ።

11. ጥፋት በመካከሏ ይገኛል፤ግፍና አታላይነትም ከጎዳናዋ አይጠፋም።

12. የሚዘልፈኝ ጠላት አይደለምና፤ቢሆንማ ኖሮ በታገሥሁት ነበር፤የሚጠላኝ፣ ራሱንም ቀና ቀና ያደረገብኝ ባላንጣ አይደለም፤ቢሆንማ ከእርሱ በተሸሸግሁ ነበር።

13. ነገር ግን አድራጊው አንተ ነህ፤ እኩያዬ፣ ባልንጀራዬና ወዳጄ፤

14. በእግዚአብሔርም ቤት አብረን በሕዝብ መካከል ተመላለስን፤ደስ የሚል ፍቅር በአንድነት ነበረን።

15. ሞት ሳይታሰብ ድንገት ይምጣባቸው፤በሕይወት ሳሉ ወደ ሲኦል ይውረዱ፤ክፋት በመካከላቸው አድራለችና።

16. እኔ ግን ወደ እግዚአብሔር እጣራለሁ፤ እግዚአብሔርም ያድነኛል።

17. በማታ፣ በጥዋትና በቀትር፣እጮኻለሁ፤ እቃትታለሁም፤እርሱም ድምፄን ይሰማል።

18. በተቃውሞ የተነሡብኝ ብዙዎች ናቸውና፣ከተቃጣብኝ ጦርነት፣ነፍሴን በሰላም ይቤዣታል።

19. አካሄዳቸውን አልቀየሩምና፣እግዚአብሔርንም አልፈሩትምና፣ከጥንት ጀምሮ በዙፋኑ ላይ ያለ አምላክ፣ ሴላሰምቶ ያዋርዳቸዋል።

20. ባልንጀራዬ የምለው ሰው እጁንበወዳጆቹ ላይ ሰነዘረ፤ቃል ኪዳኑንም አፈረሰ።

21. አፉ ከቅቤ ይልቅ የለዘበ ነው፤በልቡ ግን ጦርነት አለ፤ቃሉ ከዘይት ይልቅ የለሰለሰ ነው፤ይሁን እንጂ የተመዘዘ ሰይፍ ነው።

22. የከበደህን ነገር በእግዚአብሔር ላይ ጣል፤እርሱ ደግፎ ይይዝሃል፤የጻድቁንም መናወጥ ከቶ አይፈቅድም።

23. አንተ ግን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎችን ወደ ጥፋት ጒድጓድታወርዳቸዋለህ፤ደም የተጠሙ ሰዎችና አታላዮች፣የዘመናቸውን እኩሌታ አይኖሩም።እኔ ግን በአንተ እታመናለሁ።