ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የድል መዝሙር

ለመዘምራን አለቃ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ የዳዊት መዝሙር፤ ይህም እግዚአብሔር ከሳዖልና ከጠላቶቹ ሁሉ እጅ በታደገው ጊዜ፣ ለእግዚአብሔር እንዲህ ሲል የዘመረው ነው፦

1. ጒልበቴ እግዚአብሔር ሆይ፤ እወድሃለሁ።

2. እግዚአብሔር ዐለቴ፣ መጠጊያዬና ታዳጊዬ ነው፤አምላኬ የምሸሸግበት ዐለቴ፤እርሱ ጋሻዬ፣ የድነቴ ቀንድና ዐምባዬ ነው።

3. ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፤ከጠላቶቼም እድናለሁ።

4. የሞት ገመድ አነቀኝ፤የጥፋት ጐርፍም አጥለቀለቀኝ።

5. የሲኦል ገመድ ተጠመጠመብኝ፤የሞት ወጥመድም ተጋረጠብኝ።

6. በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤እንዲረዳኝም ወደ አምላኬ ጮኽሁ፤እርሱም ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤ጩኸቴም ከፊቱ ደረሰ፤ ወደ ጆሮውም ገባ።

7. ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ተናወጠችም፤የተራሮችም መሠረት ተናጋ፤ጌታ ተቈጥቶአልና ተንቀጠቀጡ።

8. ከአፍንጫው ጢስ ወጣ፤የሚባላ እሳት ከአፉ፤የፍም ነበልባል ከእርሱ ፈለቀ።

9. ሰማያትን ሰንጥቆ ወረደ፤ከእግሩም በታች ጥቍር ደመና ነበረ።

10. በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤በነፋስም ክንፍ መጠቀ።

11. ጨለማን መሰወሪያው፣ በዙሪያውም አጐበሩ አደረገው፤በዝናብ አዘል ጥቍር ደመናም ተሸፈነ።

12. በፊቱ ካለው ብርሃን የተነሣ፣ደመናት፣ የበረዶ ድንጋይና መብረቅ ወጡ።

13. እግዚአብሔር ከሰማያት አንጐደጐደ፤ልዑልም ድምፁን አስተጋባ።

14. ፍላጻውን አስፈንጥሮ በተናቸው፤መብረቅ አዥጐድጒዶ አሳደዳቸው።

15. እግዚአብሔር ሆይ፤ ከተግሣጽህ የተነሣ፣ከአፍንጫህም እስትንፋስ የተነሣ፣የባሕር ወለል ተገለጠ፤የዓለምም መሠረት ራቍቱን ቀረ።

16. ከላይ እጁን ወደ ታች ዘርግቶ ያዘኝ፤ከብዙ ጥልቅ ውሃም አወጣኝ፤

17. ከኀያላን ጠላቶቼ አዳነኝ፤ከእኔ ከሚበረቱ ባላንጣዎቼም ታደገኝ።

18. እነርሱ በመከራዬ ቀን መጡብኝ፤ እግዚአብሔር ግን ድጋፍ ሆነኝ።

19. ወደ ሰፊ ስፍራ አወጣኝ፤ደስ ተሰኝቶብኛልና አዳነኝ።

20. እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መልሶልኛል፤እንደ እጄ ንጽሕናም ከፍሎኛል፤

21. የእግዚአብሔርን መንገድ ጠብቄአለሁና፤አምላኬንም በመተው ክፉ አላደረግሁም።

22. ሕጎቹ ሁሉ በፊቴ ናቸው፤ሥርዐቱን ከፊቴ አላራቅሁም።

23. በፊቱ ነቀፋ አልነበረብኝም፤ራሴንም ከኀጢአት ጠብቄአለሁ።

24. እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መጠን፣በፊቱም እንደ እጄም ንጽሕና ከፍሎኛል።

25. ከታማኙ ጋር ታማኝ ትሆናለህ፤እንከን ከሌለበት ጋር ያለ እንከን ትሆናለህ፤

26. ከንጹሑ ጋር ንጹሕ ሆነህ ትገኛለህ፤ለጠማማው አንተ ትጠምበታለህ።

27. አንተ ትሑታንን ታድናለህ፤ትዕቢተኛውን ዐይን ግን ታዋርዳለህ።

28. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ መብራቴን ታበራለህ፤አምላኬ ሆይ፤ ጨለማዬን ብርሃን ታደርገዋለህ።

29. በአንተ ጒልበት በሰራዊት ላይ እረማመዳለሁ፤በአምላኬም ኀይል ቅጥር እዘላለሁ።

30. የአምላክ መንገድ ፍጹም ነው፤ የእግዚአብሔር ቃል የነጠረ ነው።መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ፣እርሱ ጋሻ ነው።

31. ከእግዚአብሔር በቀር ማን አምላክ አለ?ከአምላካችንስ በቀር ዐምባ ማን ነው?

32. ኀይልን የሚያስታጥቀኝ፣መንገዴንም የሚያቃና እግዚአብሔር ነው።

33. እርሱ እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች ያደርጋል፤በከፍታዎችም ላይ ያቆመኛል።

34. እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናቸዋል፤ክንዴም የናስ ቀስት መገተር ይችላል።

35. የድል ጋሻ ሰጥተኸኛል፤ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች፤ዝቅ ብለህም ከፍ አደረግኸኝ።

36. ከሥሬ ያለውን ስፍራ ለአረማመዴ አሰፋህልኝ፤እግሬም አልተንሸራተተም።

37. ጠላቶቼን አሳድጄ ያዝኋቸው፤እስኪጠፉም ወደ ኋላዬ አልተመለስሁም።

38. እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቀቅኋቸው፤ከእግሬም ሥር ወደቁ።

39. አንተ ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፤ባላንጦቼ እግሬ ላይ እንዲደፉ አደረግህ።

40. ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው እንዲሸሹ አደረግህ፤እኔም የሚጠሉኝን አጠፋኋቸው።

41. ለርዳታ ጮኹ፤ የሚያስጥላቸው ግን አላገኙም፤ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም አልመለሰላቸውም።

42. ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ አደቀቅኋቸው፤እንደ መንገድ ላይ ጭቃም አውጥቼ ጣልኋቸው።

43. ከሕዝብ ግርግር አወጣኸኝ፤የሕዝቦች መሪ አድርገህ አስቀመጥኸኝ፤የማላውቀውም ሕዝብ ተገዛልኝ።

44. ትእዛዜን እንደ ሰሙ ይታዘዙልኛል፤ባዕዳንም በፊቴ አንገት ደፉ።

45. ባዕዳን በፍርሃት ተዋጡ፤ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ።

46. እግዚአብሔር ሕያው ነው! ዐምባዬ ይባረክ፤ያዳነኝ አምላክ ከፍ ከፍ ይበል።

47. እርሱ በቀሌን የሚመልስልኝ፣ሕዝቦችንም የሚያስገዛልኝ አምላክ ነው፤

48. ከጠላቶቼም የሚታደገኝ እርሱ ነው።አንተ ከባላንጦቼ በላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ፤ከጨካኞች አዳንኸኝ።

49. እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለዚህ በአሕዛብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤ስምህንም በመዝሙር እወድሳለሁ።

50. እርሱ ላነገሠው ታላላቅ ድሎችን ይሰጣል፤ጽኑ ፍቅሩንም ለቀባው፣ለዳዊትና ለዘሩ ለዘላለም ይገልጣል።