ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48
  49. 49
  50. 50
  51. 51
  52. 52
  53. 53
  54. 54
  55. 55
  56. 56
  57. 57
  58. 58
  59. 59
  60. 60
  61. 61
  62. 62
  63. 63
  64. 64
  65. 65
  66. 66
  67. 67
  68. 68
  69. 69
  70. 70
  71. 71
  72. 72
  73. 73
  74. 74
  75. 75
  76. 76
  77. 77
  78. 78
  79. 79
  80. 80
  81. 81
  82. 82
  83. 83
  84. 84
  85. 85
  86. 86
  87. 87
  88. 88
  89. 89
  90. 90
  91. 91
  92. 92
  93. 93
  94. 94
  95. 95
  96. 96
  97. 97
  98. 98
  99. 99
  100. 100
  101. 101
  102. 102
  103. 103
  104. 104
  105. 105
  106. 106
  107. 107
  108. 108
  109. 109
  110. 110
  111. 111
  112. 112
  113. 113
  114. 114
  115. 115
  116. 116
  117. 117
  118. 118
  119. 119
  120. 120
  121. 121
  122. 122
  123. 123
  124. 124
  125. 125
  126. 126
  127. 127
  128. 128
  129. 129
  130. 130
  131. 131
  132. 132
  133. 133
  134. 134
  135. 135
  136. 136
  137. 137
  138. 138
  139. 139
  140. 140
  141. 141
  142. 142
  143. 143
  144. 144
  145. 145
  146. 146
  147. 147
  148. 148
  149. 149
  150. 150

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 22 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

የጻድቅ ሰው መከራና ተስፋ

ለመዘምራን አለቃ፤ በ“ንጋት አጋዘን” ዜማ የሚዜም፤ የዳዊት መዝሙር

1. አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውኸኝ?እኔን ከማዳን፣ከመቃተቴም ቃል ለምን ራቅህ?

2. አምላኬ ሆይ፤ በቀን ወደ አንተ አጮኻለሁ፤አንተ ግን አልመለስህልኝም፤በሌሊት እንኳ አላረፍሁም።

3. አንተ ግን ቅዱሱ ነጋሢ፤የእስራኤልም ምስጋና ነህ።

4. አባቶቻችን በአንተ ታመኑ፤ተማመኑብህ፤ አንተም ታደግሃቸው።

5. ወደ አንተ ጮኹ፤ ዳኑም፤በአንተም ታመኑ፤ አላፈሩም።

6. እኔ ግን ትል እንጂ ሰው አይደለሁም፤ሰው ያላገጠብኝ፣ ሕዝብም የናቀኝ ነኝ።

7. የሚያዩኝ ሁሉ ይሣለቁብኛል፤ራሳቸውንም እየነቀነቁ እንዲህ እያሉ ይዘልፉኛል፤

8. “በእግዚአብሔር ተማምኖአል፤እንግዲህ እርሱ ያድነው፤ደስ የተሰኘበትን፣እስቲ ይታደገው።”

9. አንተ ግን ከማሕፀን አወጣኸኝ፤በእናቴም ጡት ሳለሁ፣ መታመኛ ሆንኸኝ።

10. ከማሕፀን ስወጣም በአንተ ላይ ተጣልሁ፤ከእናቴ ሆድ ጀምሮም አንተ አምላኬ ነህ።

11. መከራ እየተቃረበ ነውና፣የሚረዳኝም የለምና፣ከእኔ አትራቅ።

12. ብዙ ኰርማዎች ከበቡኝ፤ኀይለኛ የባሳን በሬዎችም ዙሪያዬን ቆሙ።

13. እንደሚነጥቅና እንደሚያገሣ አንበሳ፣አፋቸውን ከፈቱብኝ።

14. እንደ ውሃ ፈሰስሁ፤ዐጥንቶቼም ሁሉ ከመጋጠሚያቸው ወለቁ፤ልቤ እንደ ሰም ሆነ፤በውስጤም ቀለጠ።

15. ጒልበቴ እንደ ገል ደረቀ፤ምላሴ ከላንቃዬ ጋር ተጣበቀ፤ወደ ሞት ዐፈርም አወረድኸኝ።

16. ውሾች ከበቡኝ፤የክፉዎች ሸንጎ በዙሪያዬ ተሰልፎአል፤እጆቼንና እግሮቼንም ቸነከሩኝ።

17. ዐጥንቶቼን ሁሉ አንድ በአንድ መቍጠር እችላለሁ፤እነርሱም አፍጥጠው ይመለከቱኛል።

18. ልብሶቼን ተከፋፈሉ፤በእጀ ጠባቤም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።

19. አንተ ግን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ከእኔ አትራቅ፤አጋዤ ሆይ፤ እኔን ለመርዳት ፍጠን።

20. ነፍሴን ከሰይፍ ታደጋት፤ውድ ሕይወቴንም ከውሾች ጡጫ አድናት።

21. ከአንበሶች አፍ አድነኝ፤ከአውራሪስ ቀንድም ታደገኝ።

22. ስምህን ለወንድሞቼ እነግራለሁ፤በጉባኤም መካከል አመሰግንሃለሁ።

23. እናንተ እግዚአብሔርን የምትፈሩ፤አወድሱት፤እናንተ የያቆብ ዘር ሁላችሁ፤ አክብሩት፤የእስራኤልም ዘር ሁላችሁ፤ እርሱን ፍሩት።

24. እርሱ የተጨነቀውን ሰው ጭንቀት፣አልናቀም፤ ቸልም አላለምና፤ፊቱንም ከእርሱ አልሰወረም፤ነገር ግን ድረስልኝ ብሎ ሲጮኽ ሰማው።

25. በታላቅ ጉባኤ የማቀርበው ምስጋናዬ ከአንተ የመጣ ነው፤እርሱን በሚፈሩት ፊት ስእለቴን እፈጽማለሁ።

26. ምስኪኖች በልተው ይጠግባሉ፤ እግዚአብሔርን የሚሹትም ያመሰግኑታል፤ልባችሁም ለዘላለም ሕያው ይሁን!

27. የምድር ዳርቻዎች ሁሉ ያስታውሳሉ፤ወደ እግዚአብሔርም ይመለሳሉ፤የሕዝቦች ነገዶች ሁሉ፣በፊቱ ይሰግዳሉ።

28. መንግሥት የእግዚአብሔር ናትና፤ሕዝቦችንም የሚገዛ እርሱ ነው።

29. የምድር ከበርቴዎች ይበላሉ፤ይሰግዱለታልም፤ነፍሱን በሕይወት ማቆየት የማይችለው፣ ወደ ዐፈር፣ተመላሽ የሆነው ሁሉ በፊቱ ይንበረከካል።

30. የኋለኛው ትውልድ ያገለግለዋል፤ለመጪው ትውልድ ስለ ጌታ ይነገረዋል።

31. ገና ላልተወለደ ሕዝብ፣ጽድቁን ይነግራሉ፤እርሱ ይህን አድርጎአልና።