ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 30:2-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የነገርሁህን ቃል ሁሉ በመጽሐፍ ጻፈው።

3. እነሆ፣ ሕዝቤን እስራኤልንና ይሁዳን’ ይላል እግዚአብሔር፤ ‘ለአባቶቻቸው ወደ ሰጠኋት ምድር የምመልስበት ጊዜ ተቃርቦአል፤ እነርሱም ይወርሷታል’ ይላል እግዚአብሔር።”

4. እግዚአብሔር ስለ እስራኤልና ስለ ይሁዳ የተናገረው ቃል ይህ ነው፤

5. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘የፍርሀትና የሽብር ጩኸት ተሰምቶአል፤ሰላምም የለም።

6. እስቲ ጠይቁ፤ ተመልከቱም፤ወንድ መውለድ ይችላል?ታዲያ ወንድ ሁሉ ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣እጁን በሆዱ ላይ አድርጎ፣የሰውስ ሁሉ ፊት ጠቍሮ የማየው ለምንድን ነው?

7. ያ ቀን ምንኛ አስጨናቂ ይሆናል!እንደዚያም ያለ አይኖርም፤ለያዕቆብ የመከራ ጊዜ ነው፤ነገር ግን ይተርፋል።

8. “ ‘በዚያን ቀን’ ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤‘በጫንቃቸው ላይ ያለውን ቀንበር እሰብራለሁ፤እስራታቸውንም እበጥሳለሁ፤ከእንግዲህ ባዕዳን አይገዙአቸውም።

9. ነገር ግን ለአምላካቸው ለእግዚአብሔር፣ለማስነሣላቸውም ለንጉሣቸው፣ለዳዊት ይገዛሉ።

10. “ ‘ስለዚህ፤ አገልጋዬ ያዕቆብ ሆይ፤ አትፍራ፤እስራኤል ሆይ፤ አትደንግጥ፤’ይላል እግዚአብሔር፤‘አንተን ከሩቅ አገር፣ዘርህንም ከተማረኩበት ምድር እታደጋለሁ፤ያዕቆብ ተመልሶ በሰላምና በርጋታ ይቀመጣል፣የሚያስፈራውም አይኖርም።

11. እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፤ አድንሃለሁም፣ይላል እግዚአብሔር፤‘በአሕዛብ መካከል በትኜሃለሁ፤እነዚህን አሕዛብ ሁሉ ፈጽሜ አጠፋለሁ፤አንተን ግን ሙሉ በሙሉ አላጠፋህም፤በመጠኑ እቀጣሃለሁ እንጂ፣ያለ ቅጣት አልተውህም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 30