ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 66:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ሰማይ ዙፋኔ ነው፤ምድርም የእግሬ ማረፊያ ናት፤ታዲያ የምትሠሩልኝ ቤት፣የማርፍበትስ ስፍራ የቱ ነው?

2. እነዚህን ነገሮች ሁሉ እጄ አልሠራችምን?እንዲገኙስ ያደረግሁ እኔ አይደለሁምን?”ይላል እግዚአብሔር።“ነገር ግን እኔ ወደዚህ፣ትሑት ወደ ሆነና መንፈሱ ወደ ተሰበረ፣በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ።

3. ነገር ግን ወይፈን የሚሰዋልኝ፣ሰው እንደሚገድል ነው፤የበግ ጠቦት የሚያቀርብልኝ፣የውሻ ዐንገት እንደሚሰብር ሰው ነው፤የእህል ቍርባን የሚያዘጋጅልኝ፣የዕሪያ ደም እንደሚያቀርብልኝ ሰው ነው፤የመታሰቢያን ዕጣን የሚያጥንልኝም፣ጣዖትን እንደሚያመልክ ሰው ነው፤የገዛ መንገዳቸውን መርጠዋል፤ነፍሳቸውም በርኵሰታቸው ደስ ይላታል።

4. ስለዚህ ችግር እንዲደርስባቸው አደርጋለሁ፤የፈሩትንም አመጣባቸዋለሁ፤በተጣራሁ ጊዜ የመለሰ፣በተናገርሁ ጊዜ ያደመጠ ሰው የለምና።በፊቴ ክፉ ነገር አደረጉ፤የሚያስከፋኝንም መረጡ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 66