ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 51:6-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. ዐይኖቻችሁን ወደ ሰማያት አንሡ፤ወደ ታች ወደ ምድርም ተመልከቱ፤ሰማያት እንደ ጢስ በነው ይጠፋሉ፤ምድር እንደ ልብስ ታረጃለች፤ነዋሪዎቿም እንደ አሸን ፈጥነው ይረግፋሉ፤ማዳኔ ግን ለዘላለም ይኖራል፤ጽድቄም መጨረሻ የለውም።

7. “እናንት ጽድቅን የምታውቁ፣ሕጌንም በልባችሁ ያኖራችሁ ሰዎች ስሙኝ፤ሰዎች ሲዘብቱባችሁ አትፍሩ፤ሲሰድቧችሁ አትደንግጡ።

8. ብል እንደ ልብስ ይበላቸዋል፤ትል እንደ በግ ጠጒር ይውጣቸዋል፤ጽድቄ ግን ለዘላለም፣ማዳኔም ከትውልድ እስከ ትውልድ ጸንታ ትኖራለች።”

9. የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፤ተነሥ፤ ተነሥ! ኀይልን ልበስ፤እንዳለፉት ዘመናት፣በጥንት ትውልዶችም እንደሆነው ሁሉ ተነሥ።ረዓብን የቈራረጥህ፣ታላቁን ዘንዶ የወጋህ አንተ አይደለህምን?

10. የዳኑት እንዲሻገሩ ባሕሩን፣የታላቁን ጥልቅ ውሆች ያደረቅህ፣በጥልቁም ውስጥ መንገድ ያበጀህ፣አንተ አይደለህምን?

11. እግዚአብሔር የተቤዣቸው ይመለሳሉ፤በዝማሬ ወደ ጽዮን ይገባሉ፤የዘላለማዊ ደስታን አክሊል ይቀዳጃሉ፤ተድላና ደስታ ያገኛሉ፤ሐዘንና ልቅሶም ከእነርሱ ይሸሻል።

12. “የማጽናናችሁ እኔ፣ እኔው ብቻ ነኝ፤ሟች የሆኑትን ሰዎች፣እንደ ሣር የሚጠወልጉትን የሰው ልጆችለምን ትፈራለህ?

13. የፈጠረህን፣ሰማያትን የዘረጋውን፣ምድርን የመሠረተውን እግዚአብሔርን ረስተሃል፤ሊያጠፋህ ከተዘጋጀው፣ከጨቋኙ ቊጣ የተነሣ፣በየቀኑ በሽብር ትኖራለህ፤ታዲያ የጨቋኙ ቊጣ የት አለ?

14. ዐንገታቸውን የደፉ እስረኞች በፍጥነት ነጻ ይወጣሉ፤በታሰሩበትም ጒድጓድ ውስጥ አይሞቱም፤እንጀራ አያጡም።

15. ሞገዱ እንዲተም ባሕሩን የማናውጥ፣እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝና፤ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው።

16. ቃሌን በአፍህ አኖርሁ፤በእጄ ጥላ ጋረድሁህ፤ሰማያትን በስፍራቸው ያስቀመጥሁ፣ምድርን የመሠረትሁ፣ጽዮንንም፣ ‘አንቺ ሕዝቤ ነሽ’ ያልሁ እኔ ነኝ።

17. ከእግዚአብሔር እጅ፣የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ፣ዝቃጩ እንኳ ሳይቀር፣ሰዎችን የሚያንገደግደውን ዋንጫ የጨለጥሽ፣ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ፤ተነሺ፤ ተነሺ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 51