ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 42:3-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. የተቀጠቀጠ ሸምበቆ አይሰብርም፤የሚጤስም የጧፍ ክር አያጠፋም፤ፍትሕን በታማኝነት ያመጣል።

4. ፍትሕን በምድር እስኪያመጣ ድረስ፣አይደክምም፤ ተስፋም አይቈርጥም፤ደሴቶች በሕጉ ይታመናሉ።”

5. ሰማያትን የፈጠረ፣ የዘረጋቸውም፣ምድርንና በውስጧ ያሉትን ሁሉ ያበጀ፣ለሕዝቧ እስትንፋስን፣ለሚኖሩባትም ሕይወትን የሚሰጥ፣ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

6. “እኔ እግዚአብሔር በጽድቅ ጠርቼሃለሁ፤እጅህንም እይዛለሁ፤እጠብቅሃለሁ፤ለሕዝቡ ቃል ኪዳን፣ለአሕዛብም ብርሃን አደርግሃለሁ።

7. የዕውሮችን ዐይን ትከፍታለህ፤ምርኮኞችን ከእስር ቤት፣በጨለማ የተቀመጡትንም ከወህኒ ታወጣለህ።

8. “እኔ እግዚአብሔር ነኝ፤ ስሜም ይህ ነው፤ክብሬን ለሌላ፣ምስጋናዬንም ለጣዖት አልሰጥም።

9. እነሆ፤ የቀድሞው ነገር ተፈጽሞአል፤እኔም አዲስ ነገር እናገራለሁ፤ከመብቀሉም በፊት፣ለእናንተ አስታውቃለሁ።

10. እናንት ወደ ባሕር የምትወርዱ፣ በዚያም ያላችሁ ሁሉ፣ደሴቶችና በዚያ የምትኖሩ በሙሉ፣ ለእግዚአብሔር አዲስ መዝሙር፣ከምድር ዳርቻም ምስጋናውን ዘምሩ።

11. ምድረ በዳውና ከተሞቹ ድምፃቸውን ከፍ ያድርጉ፤ቄዳር ያለችበት መንደር ደስ ይበለው፤የሴላ ሕዝቦች በደስታ ይዘምሩ፤ከተራሮችም ራስ ላይ ይጩኹ።

12. ክብር ለእግዚአብሔር ይስጡ፤ምስጋናውንም በደሴቶች ያውጁ።

13. እግዚአብሔር እንደ ኀያል ሰው ይዘምታል፤እንደ ተዋጊ በወኔ ይነሣል፤የቀረርቶ ጩኸት ያሰማል፤ጠላቶቹንም ድል ያደርጋል።

14. “ለረጅም ጊዜ ዝም አልሁ፤ጸጥ አልሁ፤ ራሴንም ገታሁ፤አሁን ግን ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣እጮኻለሁ፤ ቁና ቁና እቃትታለሁ፤ እተነፍሳለሁ።

15. ተራራውንና ኰረብታውን አፈርሳለሁ፤ዕፀዋቱን ሁሉ አደርቃለሁ፤ወንዙንም ደሴት አደርጋለሁ፤ኵሬውን አደርቃለሁ።

16. ዕውሮችን በማያወቁት መንገድእመራቸዋለሁ፤ባልተለመደ ጐዳና እወስዳቸዋለሁ።ጨለማውን በፊታቸው ብርሃን አደርጋለሁ፤ጐርባጣውን ስፍራ አስተካክላለሁ።ይህን አደርጋለሁ፤አልተዋቸውም።

17. በጣዖት የሚታመኑ ግን፣ምስሎችን፣ ‘አምላኮቻችን ናችሁ’ የሚሉ፣ወደ ኋላቸው ይመለሳሉ፤ ፈጽመው ይዋረዳሉም።

18. “እናንት ደንቈሮዎች ስሙ፤እናንት ዕውሮች እዩ፤ ተመልከቱም።

19. አገልጋዬ እንጂ፣ ሌላ ዕውር ማን አለ?ከምልከው መልእክተኛዬስ በቀር ማን ደንቈሮ አለ?ለእኔ ታማኝ እንደሆነ ሰው የታወረ፣እንደ እግዚአብሔርስ አገልጋይ ዕውር ማነው?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 42