ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 41:2-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. “ከምሥራቅ አንዱን ያነሣው፣በጽድቅም ወደ አገልግሎቱ የጠራው ማን ነው?አሕዛብን አሳልፎ ሰጠው፤ነገሥታትን በፊቱ አስገዛለትበሰይፉም እንደ ትቢያ አቦነናቸው፤በቀስቱም በነፋስ እንደ ተበተነ ገለባ አደረጋቸው።

3. አሳደዳቸው ያለ ችግር ዐልፎ ሄደ፤እግሩም ቀድሞ ባልረገጠው መንገድ ተጓዘ።

4. ይህን የሠራና ያደረገ፣ትውልድን ከጥንት የጠራ ማን ነው?እኔ እግዚአብሔር ከፊተኛው፣ከኋለኛውም ጋር፤ እኔው ነኝ።”

5. ደሴቶች አይተው ፈሩ፤የምድር ዳርቾች ደነገጡ፤ቀረቡ፤ ወደ ፊትም መጡ።

6. እያንዳንዱ ይረዳዳል፤ወንድሙንም፣ “አይዞህ” ይለዋል።

7. ባለጅ የወርቅ አንጥረኛውን ያበረታታዋል፤በመዶሻ የሚያሳሳውም፣በመስፍ ላይ የሚቀጠቅጠውን ያነቃቃዋል፤ስለ ብየዳም ሥራው፣ “መልካም ነው” ይለዋል፤የጣዖቱ ምስል እንዳይወድቅም በምስማር ያጣብቀዋል።

8. “አንተ ግን፣ ባሪያዬ እስራኤል፣የመረጥሁ ያዕቆብ፣የወዳጄ የአብርሃም ዘር ሆይ፤

9. ከምድር ዳርቻ ያመጣሁህ፣ከአጥናፍም የጠራሁህ፣‘አንተ ባሪያዬ ነህ’ ያልሁህ፤መረጥሁህ እንጂ፤ አልጣልሁህም።

10. እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤አምላክህ ነኝና አትደንግጥ።አበረታሃለሁ፤ እረዳሃለሁ፤በጽድቄም ቀኝ እጄ ደግፌ እይዝሃለሁ።

11. “እነሆ፤ የተቈጡህ ሁሉ፣እጅግ ያፍራሉ፤ ይዋረዳሉም፤የሚቋቋሙህ፣እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤ ይጠፋሉም።

12. ጠላቶችህን ብትፈልጋቸው እንኳ፣አታገኛቸውም፤የሚዋጉህም፣እንዳልነበሩ ይሆናሉ።

13. እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ‘አትፍራ፤እረዳሃለሁ’ብዬ ቀኝ እጅህን እይዛለሁና።

14. አንት ትል ያዕቆብ፣ታናሽ እስራኤል ሆይ፤‘አትፍራ እኔ እረዳሃለሁ’ ” ይላል እግዚአብሔር፤የሚቤዥህ የእስራኤል ቅዱስ ነው።

15. “እነሆ፣ አዲስየተሳለና ብዙ ጥርስ ያለው ማሄጃ አደርግሃለሁ፤ተራሮችን ታሄዳለህ፤ ታደቃቸዋለህ፤ኰረብቶችንም ገለባ ታደርጋቸዋለህ።

16. ታበጥራቸዋለህ፤ ነፋስ ጠርጎ ይወስዳቸዋል፤ዐውሎ ነፋስም ይበትናቸዋል።አንተ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል፤በእስራኤል ቅዱስ ሞገስ ታገኛለህ።

17. “ድኾችና ችግረኞች ውሃ ይፈልጋሉ፤ዳሩ ግን ምንም አያገኙም፤ጒሮሮአቸው በውሃ ጥም ደርቆአል።ነገር ግን እኔ እግዚአብሔር እመልስላቸዋለሁ፤እኔ የእስራኤል አምላክ አልተዋቸውም።

18. በተራቈቱ ኰረብቶች ላይ ወንዞችን፣በሸለቆዎች ውስጥ ምንጮች አፈልቃለሁ።ምድረ በዳውን የውሃ ኵሬ፣የተጠማውን ምድር የውሃ ምንጭ አደርጋለሁ።

19. በምድረ በዳ፣ዝግባን፣ ግራርን፣ ባርሰነትንና ወይራን አበቅላለሁ፤በበረሃ፣ ጥድን፣ አስታንናሸውሸዌን በአንድነት እተክላለሁ።

20. ስለዚህ ሰዎች ያያሉ፤ ያውቃሉ፤ የእግዚአብሔር እጅ ይህን እንዳደረገ፣የእስራኤል ቅዱስ እንደ ፈጠረው፣በአንድነት ይገነዘባሉ፤ ያስተውላሉም።

21. “ሙግታችሁን ይዛችሁ ቅረቡ” ይላል እግዚአብሔር፤“ማስረጃችሁን አምጡ” ይላል የያዕቆብ ንጉሥ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 41