ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢሳይያስ 1:1-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን፣ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ፤

2. ሰማያት ሆይ፤ ስሙ! ምድር ሆይ፤ አድምጪ! እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሮአልና፤“ልጆች ወለድሁ፣ አሳደግኋቸውም፤እነርሱ ግን ዐመፁብኝ።

3. በሬ ጌታውን፣አህያ የባለቤቱን ጋጥ ያውቃል፤እስራኤል ግን አላወቀም፤ሕዝቤም አላስተዋለም።”

4. እናንተ ኀጢአተኛ ሕዝብ፣በደል የሞላበት ወገን፣የክፉ አድራጊ ዘር፣ምግባረ ብልሹ ልጆች ወዮላችሁ እግዚአብሔርን ትተዋል፤የእስራኤልን ቅዱስ አቃለዋል፤ጀርባቸውንም በእርሱ ላይ አዙረዋል።

5. ለምን ዳግመኛ ትመታላችሁ?ለምንስ በዐመፅ ትጸናላችሁ?ራሳችሁ በሙሉ ታሞአል፤ልባችሁ ሁሉ ታውኮአል።

6. ከእግር ጥፍራችሁ እስከ ራስ ጠጒራችሁጤና የላችሁም፤ቍስልና ዕባጭ እንዲሁም እዥ ብቻ ነው፤አልታጠበም፤ አልታሰረም፤በዘይትም አልለዘበም።

7. አገራችሁ ባድማ፣ከተሞቻችሁ በእሳት የተቃጠሉ ይሆናሉ፤ዐይናችሁ እያየ፣መሬታችሁ በባዕድ ይነጠቃል፤ጠፍም ይሆናል።

8. የጽዮን ሴት ልጅበወይን አትክልት ውስጥ እንዳለ ዳስ፣በዱባ ተክል ወስጥ እንደሚገኝ ጐጆ፣እንደ ተከበበም ከተማ ተተወች።

9. የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፣እንደ ሰዶም በሆንንገሞራንም በመሰልን ነበር።

10. እናንተ የሰዶም ገዦች፤የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤እናንተ የገሞራ ሰዎች፤ የእግዚአብሔርን ሕግ አድምጡ።

11. “የመሥዋዕታችሁ ብዛትለእኔ ምኔ ነው?” ይላል እግዚአብሔር።“የሚቃጠለውን የአውራ በግናየሰቡ እንስሳትን ስብ ጠግቤአለሁ፤በበሬ፣ በበግ ጠቦትና በፍየል ደም ደስአልሰኝም።

12. በፊቴ ለመቅረብ ስትመጡ፣ይህን ሁሉ እንድታመጡ፣የመቅደሴን ደጅ እንድትረግጡ ማን ጠየቃችሁ?

13. ከንቱውን መባ አታቅርቡ፤ዕጣናችሁን እጸየፋለሁ፤የወር መባቻ በዓላችሁን፣ሰንበቶቻችሁን፣ ጉባኤያችሁንናበክፋት የተሞላውን ስብሰባችሁን መታገሥአልቻልሁም።

14. የወር መባቻችሁንና የተደነገጉ በዓሎቻችሁንነፍሴ ጠልታለች፤ሸክም ሆነውብኛል፤መታገሥም አልቻልሁም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢሳይያስ 1