ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ራእይ 12:9-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ታላቁ ዘንዶ፣ የጥንቱ እባብ ተጣለ፤ እርሱም ዲያብሎስ ወይም ሰይጣን ተብሎ የሚጠራው፣ ዓለምን ሁሉ የሚያስተው ነው፤ እርሱ ወደ ምድር ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ።

10. ከዚህ በኋላ ታላቅ ድምፅ በሰማይ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤“አሁን የአምላካችን ማዳን፣ ኀይልናመንግሥት፣የእርሱ ክርስቶስ ሥልጣንም መጥቶአል።ቀንና ሌሊት በአምላካችን ፊት ሲከሳቸውየነበረው፣የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና።

11. እነርሱም በበጉ ደም፣በምስክርነታቸውም ቃል፣ድል ነሡት፤እስከ ሞት ድረስ እንኳ፣ለነፍሳቸው አልሳሱም።

12. ስለዚህ ሰማያት ሆይ፣በውስጣቸውም የምትኖሩ ሆይ፣ደስ ይበላችሁ፤ምድርና ባሕር ግን ወዮላችሁ ምክንያቱም ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን ብቻእንደ ቀረው ስላወቀ፣በታላቅ ቍጣ ተሞልቶ ወደ እናንተ ወርዶአል።

13. ዘንዶው ወደ ምድር እንደተጣለ ባየ ጊዜ፣ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ራእይ 12