ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፀአት 16:4-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን አለው፤ “ከሰማይ እንጀራ አዘንብላችኋለሁ። ሕዝቡም በየቀኑ እየወጡ ለዕለት የሚበቃቸውን ይሰበስቡ፤ በዚህም ትእዛዛቴን ይጠብቁ እንደሆነ እፈትናቸዋለሁ።

5. በስድስተኛው ቀን በሌሎቹ ዕለታት ከሚሰበስቡት እጥፍ ሰብስበው ያዘጋጁ።

6. ስለዚህ ሙሴና አሮን ለእስራኤላውያን ሁሉ፣ እንዲህ አሉ፤ “ከግብፅ ምድር ያወጣችሁ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኑን በዛሬይቱ ምሽት ታውቃላችሁ።

7. በእርሱ ላይ ያሰማችሁትን ማጒረምረም ሰምቷልና በማለዳ እግዚአብሔርን (ያህዌ) ክብር ታያላችሁ፤ ለመሆኑ በእኛስ ላይ የምታጒረመርሙት እኛ ምንድን ነንና ነው?” አሏቸው።

8. ሙሴም ንግግሩን በመቀጠል፣ “በእርሱ ላይ ማጒረምረማችሁን ሰምቶአልና በምሽት የምትበሉትን ሥጋ፣ በማለዳም የምትፈልጉትን ያህል እንጀራ በሚሰጣችሁ ጊዜ እግዚአብሔር (ያህዌ) መሆኑን ታውቃላችሁ፤ እኛ ማን ነን? በእኛ ላይ አይደለም ያጒረመረማችሁት፤ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ላይ ነው እንጂ” አላቸው።

9. ከዚያም ሙሴ አሮንን፣ “ ‘ማጒረምረማችሁን እርሱ ሰምቶአልና ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት ቅረቡ’ ብለህ ለመላው የእስራኤል ማኅበር ተናገር” አለው።

10. አሮንም ለመላው የእስራኤል ማኅበር ሲናገር ሳለ ወደ ምድረ በዳው ተመለከቱ፤ በዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ክብር በደመናው ላይ ተገልጦ ይታይ ነበር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፀአት 16