ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 26:56-61 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

56. እያንዳንዱም ርስት በትል ልቆቹና በትንንሾቹ ነገዶች መካከል በዕጣ ይደለደላል።

57. በየጐሣቸው የተቈጠሩት ሌዋውያን እነዚህ ነበሩ፤በጌድሶን በኩል፣ የጌድሶናውያን ጐሣ፣በቀዓት በኩል፣ የቀዓታውያን ጐሣ፣በሜራሪ በኩል፣ የሜራራውያን ጐሣ፤

58. እነዚህም ደግሞ የሌዊ ጐሣዎች ነበሩ፤የሊብናውያን ጐሣ፣የኬብሮናውያን ጐሣ፣የሞሖላውያን ጐሣ፣የሙሳውያን ጐሣ፣የቆሬያውያን ጐሣ።ቀዓት የእንበረም ቅድመ አያት ነበር፤

59. ሚስቱ ዮካብድ ትባል ነበር፤ እርሷም በግብፅ አገር ከሌዋውያን የተወለደች የሌዊ ዘር ነበረች። ከእንበረምም አሮንን፣ ሙሴንና እኅታቸውን ማርያምን ወለደች።

60. አሮንም የናዳብና የአብዮድ፣ የአልዓዛርና የኢታምር አባት ነበር።

61. ነገር ግን ናዳብና አብዩድ ባልተፈቀደ እሳት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት ስላቀረቡ ሞቱ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 26