ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 50:40-43 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

40. እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን፤በዙሪያቸውም የነበሩትን ከተሞች ያለ ነዋሪ እንዳስቀራቸው”ይላል እግዚአብሔር፤“እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፣የሚቀመጥባትም አይገኝም።

41. “እነሆ፤ ሰራዊት ከሰሜን ይመጣል፤አንድ ኀያል መንግሥትና ብዙ ነገሥታት፣ከምድር ዳርቻ ተነሣሥተዋል።

42. ቀስትና ጦር ይዘዋል፤ጨካኞች ናቸው፤ ምሕረትም አያደርጉም፤በፈረሳቸው እየጋለቡ ሲመጡ፣ድምፃቸው እንደ ባሕር ሞገድ ይተማል፤ ያስገመግማል።አንቺ የባቢሎን ሴት ልጅ ሆይ፤ለጦርነት እንደ ተዘጋጁ ተዋጊዎች ይመጡብሻል።

43. የባቢሎን ንጉሥ ስለ እነርሱ ሰማ፤እጆቹም በድን ሆኑ፤ጭንቀት ይዞታል፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት ታሟል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 50