ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኤርምያስ 49:4-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. አንቺ ከዳተኛ ልጅ ሆይ፣በሸለቆችሽ ለምን ትመኪያለሽ?ለምንስ በፍሬያማ ሸለቆሽ ትኵራሪያለሽ?በብልጽግናሽ ተማምነሽ፣‘ማን ሊነካኝ ይችላል?’ ትያለሽ።

5. በዙሪያሽ ካሉት ሁሉ ዘንድ፣ሽብር አመጣብሻለሁ፤”ይላል የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤“እያንዳንዳችሁ ትሰደዳላችሁ፤በሽሽት ላይ ያሉትንም የሚሰበስብ አይገኝም።

6. “ከዚያ በኋላ ግን፣ የአሞናውያንን ምርኮ እመልሳለሁ፣”ይላል እግዚአብሔር።

7. ስለ ኤዶም፤የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ጥበብ ከቴማን ጠፍቶአልን?ምክር ከአስተዋዮች ርቆአልን?ጥበባቸውስ ተሟጧልን?

8. ዔሳውን በምቀጣ ጊዜ፣ጥፋት ስለማመጣበት፣እናንተ በድዳን የምትኖሩ ሆይ፤ወደ ኋላ ተመልሳችሁ ሽሹ፤ ጥልቅ ጒድጓድ ውስጥ ተደበቁ።

9. ወይን ለቃሚዎች ወዳንተ ቢመጡ፣ጥቂት ወይን አያስቀሩምን?ሌቦችስ በሌሊት ቢመጡ፣የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ብቻ አይደለምን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኤርምያስ 49