ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢያሱ 3:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ኢያሱም ማልዶ ተነሣ፤ ከእስራኤላውያንም ሁሉ ጋር ከሰጢም ወደ ዮርዳኖስ መጥተው፣ ወንዙን ከመሻገራቸው በፊት በዚያ ሰፈሩ።

2. ከሦስት ቀን በኋላም የጦሩ አለቆች በሰፈር ውስጥ አለፉ፤

3. ሕዝቡንም እንዲህ ሲሉ አዘዙ፤ “ሌዋውያን ካህናቱ የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ተሸክመው ስታዩ፣ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ታቦቱን ተከተሉ፤

4. ካሁን በፊት በዚህ መንገድ ሄዳችሁ ስለማታውቁ፤ በየት በኩል መሄድ እንዳለባችሁ በዚህ ትረዳላችሁ፤ ሆኖም በታቦቱና በእናንተ መካከል የሁለት ሺህ ክንድ ያህል ርቀት ይኑር፤ ወደ ታቦቱም አትቅረቡ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢያሱ 3