ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ኢዩኤል 2:1-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በጽዮን መለከትን ንፉ፤በቅዱሱ ተራራዬም የማስጠንቀቂያውን ድምፅ አሰሙ፤በምድሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ይንቀጥቀጡ፤ የእግዚአብሔር ቀን ቀርቦአልና፤እርሱም በደጅ ነው።

2. ይህም የጨለማና የጭጋግ ቀን፣የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ነው።የንጋት ብርሃን በተራሮች ላይ እንደሚወጣ፣ኀያልና ብዙ ሰራዊት ይመጣል፤ከጥንት እንዲህ ዐይነት ከቶ አልነበረም፤በሚመጡትም ዘመናት እንዲህ ዐይነት ከቶ አይሆንም።

3. በፊታቸው፣ እሳት ይባላል፤በኋላቸውም ነበልባል ይለበልባል፤በፊታቸው ምድሪቱ እንደ ዔድን ገነት ናት፤በኋላቸውም የሚቀረው ባዶ ምድረ በዳ ነው፤ምንም አያመልጣቸውም።

4. መልካቸው እንደ ፈረስ መልክ ነው፤እንደ ጦር ፈረስም ይጋልባሉ።

5. ገለባ እንደሚበላ እንደሚንጣጣ እሳት፣ለጦርነት እንደ ተዘጋጀ ኀያል ሰራዊት፣የሠረገሎችን ድምፅ የሚመስል ድምፅ እያሰሙ፣በተራሮች ጫፍ ላይ ይዘላሉ።

6. በእነርሱ ፊት ሕዝቦች ይርዳሉ፤የሁሉም ፊት ይገረጣል።

7. እንደ ተዋጊዎች ድንገት አደጋ ይጥላሉ፤እንደ ወታደሮችም ቅጥርን ይዘላሉ፤ከመንገዳቸውም ሳይወጡ፣አቅጣጫ ይዘው ይጓዛሉ።

8. እርስ በርሳቸው አይገፋፉም፤እያንዳንዱ መስመሩን ጠብቆ ይሄዳል፤መስመራቸውን ሳይለቁ፣መከላከያውን ሰብረው ያልፋሉ።

9. ከተማዪቱን ይወራሉ፤በቅጥሩም ላይ ይዘላሉ፤በቤቶች ላይ ዘለው ይወጣሉ፤እንደ ሌባም በመስኮት ይገባሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ኢዩኤል 2